TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ድሬዳዋ ፖሊስ‼️

በድሬዳዋ ከተማ ተፈጥሮ በነበረው #አለመረጋጋት እና የተቃውሞ ቀናት ጉዳት ሳይደርስበት በሀሰት ጉዳት የደረሰበት በማስመሰልና ይህንን የሃሰት ፎቶ በማህበራዊ ድረ ገፅ በመልቀቅ ግጭቶች እንዲፈጠሩ ለማድረግ የሞከረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

በፎቶው ላይ ምስሉ የሚታየው ተጠርጣሪ #ወርሰሜ_ሀሸ_መሀመድ የተባለው ግለሰብ በፀጥታ ሀይሎች ጉዳት የደረሰበት በማስመሰል ነው በፌስቡክ ገፁ ላይ ይፋ ያደረገው ፡፡ እንደ ፖሊስ ገለፃ ግለሰቡ ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ያልደረሰበት መሆኑን ገልጾ ከእንዲህ አይነት ተግባሮች መጠበቅ እንደሚገባ ያሳሰበ ሲሆን ግለሰቡ በበኩሉ ለፖሊስ በሰጠው ቃል ይቅርታ ጠይቋል ሲል የድሬዳዋ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ዘግቧል።

ምንጭ፦ waltainfo.com
@tsegabwolde @tikvahethiopia