TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
መቀለ ሊገባ የነበረ ዘይት ተያዘ‼️

የጉምርክ አሰራርን #ሳያሟላ ወደ መቀለ ሊገባ የነበረ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የምግብ ዘይት በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገለጸ።

በኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር የመቀሌ ቅርንጫፍ የኢንተሊጀንሲና ኮንትሮባንድ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ገብረእግዚአብሄር ገብረህይወት ለኢዜአ እንዳስረዱት ዘይቱ በአራት ተሽከርካሪዎች ከነ ተሳቢያቸው ተጭኖ ከጅቡቲ ወደ መቀለ ሊገባ ሲል በቁጥጥር ሥር ውሏል። የምግብ ዘይቱ በቅጥጥር ስር የዋለው በህብረተሰቡ ጥቆማ #አሸጎዳ በተባለው አካባቢ ነው፡፡

በተለያየ መጠን የታሸገው ዘይት 159 ሺህ 360 ሊትር እንደሆነ ተናግረዋል። ዘይቱን ይዘው የመጡ ተሽከርካሪዎች የንብረቱን ዝርዝር መረጃ፣የንብረቱ ባለቤትና የጉምሩክ ይለፍ ሰነዶችን ያለመያዛቸውን አመልክተዋል።

አሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ማጣራት ከተደረገ በኋላ በጉምሩክ መመሪያ መሰረት መለቀቃቸውን የተናገሩት አስተባባሪው፣ የንብረቶቹ ባለቤቶች ግን አልቀረቡም ብለዋል።

ምንጭ፦ ኢ.ዜ.አ.
@tsegabwolde @tikvahethiopia