#Tigray
ከእገታ ማስለቀቂያ 2 ሚሊዮን ብር የተጠየቀበት ህፃን ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ተገድሎ ተጥሎ ተገኘ።
ከ5 ቀናት በፊት የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳባጉና ከተማ ቀበሌ 01 ነዋሪ የሆነው ህፃን ናኦድ ተኽላይ ብርሃነ በአጋቾች ታፍኖ መወሰዱንና አጋቾቹ ለማስለቀቅያ 2 ሚሊዮን ብር መጠየቃቸው የሚጠቅስ በህፃኑ ፎቶ የታጀበ ፅሁፍ በበርካታ የማህበራዊ የትስስር ገፆች ሲዘዋወር ነበር።
ማንነታቸው ያልታወቁ ግለሰቦች ወደ ህፃኑ ቤተሰብ ደውለው ነው የማስለቀቅያ ብሩን የጠየቁት ይላል ሲዘዋወር የቆየው ፅሁፍ።
ዛሬ ሀምሌ 25/2017 ዓ.ም የተሰማው ግን እጅግ አስደንጋጭ መርዶና ከሰውነት የወጣ የጭካኔ ተግባር ነው።
ህፃን ናኦድ ተኽላይ በጭካኔ ተገድሎ የፀጥታ አካላት በተገኙበት አስክሬኑ በፍሳሽ መተላለፍያ ቦይ ተጥሎ ተገኝቷል።
የሟች ህፃን ናኦድ ተኽላይ አስክሬን ለምርመራ ወደ ሆስፒታል መላኩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከእንዳስላሰ-ሽረ የመረጃ ምንጮቹ ለማረጋገጥ ችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ከእገታ ማስለቀቂያ 2 ሚሊዮን ብር የተጠየቀበት ህፃን ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ተገድሎ ተጥሎ ተገኘ።
ከ5 ቀናት በፊት የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳባጉና ከተማ ቀበሌ 01 ነዋሪ የሆነው ህፃን ናኦድ ተኽላይ ብርሃነ በአጋቾች ታፍኖ መወሰዱንና አጋቾቹ ለማስለቀቅያ 2 ሚሊዮን ብር መጠየቃቸው የሚጠቅስ በህፃኑ ፎቶ የታጀበ ፅሁፍ በበርካታ የማህበራዊ የትስስር ገፆች ሲዘዋወር ነበር።
ማንነታቸው ያልታወቁ ግለሰቦች ወደ ህፃኑ ቤተሰብ ደውለው ነው የማስለቀቅያ ብሩን የጠየቁት ይላል ሲዘዋወር የቆየው ፅሁፍ።
ዛሬ ሀምሌ 25/2017 ዓ.ም የተሰማው ግን እጅግ አስደንጋጭ መርዶና ከሰውነት የወጣ የጭካኔ ተግባር ነው።
ህፃን ናኦድ ተኽላይ በጭካኔ ተገድሎ የፀጥታ አካላት በተገኙበት አስክሬኑ በፍሳሽ መተላለፍያ ቦይ ተጥሎ ተገኝቷል።
የሟች ህፃን ናኦድ ተኽላይ አስክሬን ለምርመራ ወደ ሆስፒታል መላኩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከእንዳስላሰ-ሽረ የመረጃ ምንጮቹ ለማረጋገጥ ችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
5😭6.46K❤992💔932😡316😢84🕊79😱57🙏35🤔28🥰10👏7