#Peace🕊
" 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " - አሜሪካ
ከ1980ዎቹ አንስቶ ጦርነት ውስጥ የነበሩት አርሜኒያና አዘርባጃን በአሜሪካ አማካኝነት የሰላም ስምምነት ፈጽመዋል።
የአዘርባጃን ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሌቭ እና የአርሜኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሽኒያን የፈረሙት ስምምነት ለአስርት አመታት የዘለቀውን ግጭት ያስቆማል ተብሏል።
የሰላም ስምምነቱን የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሸማግለዋል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሰላም ስምምነቱን " ረጅም ጊዜ የወሰደ ታሪካዊ ስምምነት ነው " ብለውታል።
ሁለቱ ሀገራት በአወዛጋቢው የናጎርኖ ካራባህ ግዛት ጦርነት ውስጥ እንደነበሩ ያስታወሱት ትራምፕ ግጭቱን " እስከወዲያኛው ይወገዳል " በማለት ተናግረዋል።
ትራምፕ፣ " 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " ብለዋል።
በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ሀገራት የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የንግድ ግንኙነትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲጀመሩ እና ለተፈፃሚነቱ አሜሪካ ጣልቃ እንድትገባ ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
Via @ThiqahEth
" 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " - አሜሪካ
ከ1980ዎቹ አንስቶ ጦርነት ውስጥ የነበሩት አርሜኒያና አዘርባጃን በአሜሪካ አማካኝነት የሰላም ስምምነት ፈጽመዋል።
የአዘርባጃን ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሌቭ እና የአርሜኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሽኒያን የፈረሙት ስምምነት ለአስርት አመታት የዘለቀውን ግጭት ያስቆማል ተብሏል።
የሰላም ስምምነቱን የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሸማግለዋል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሰላም ስምምነቱን " ረጅም ጊዜ የወሰደ ታሪካዊ ስምምነት ነው " ብለውታል።
ሁለቱ ሀገራት በአወዛጋቢው የናጎርኖ ካራባህ ግዛት ጦርነት ውስጥ እንደነበሩ ያስታወሱት ትራምፕ ግጭቱን " እስከወዲያኛው ይወገዳል " በማለት ተናግረዋል።
ትራምፕ፣ " 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " ብለዋል።
በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ሀገራት የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የንግድ ግንኙነትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲጀመሩ እና ለተፈፃሚነቱ አሜሪካ ጣልቃ እንድትገባ ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
Via @ThiqahEth
❤577🕊114👏62🤔26😡9🥰7😱6😢5💔4🙏3