#AddisAbaba
በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ4 ኪሎ ፕላዛን ፣ የ4 ኪሎ የገበያ ማዕከልን እና የመኪና ማቆሚያን በማስመረቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል።
ፕሮጀክቱ ምን ይዟል ?
- ከመሬት በታች የተገነቡ ዘመናዊ የሆኑ 102 የስጦታ እና የአልባሳት መደብሮች፣ ካፌዎች፣ ካፍቴሪያዎች፣ ማንበቢያ ስፍራዎች፣ ሱፐር ማርኬቶች፤
- ከ100 በላይ ተሽከርካሪዎችን በአንድ ጊዜ የሚያስተናግድ የመኪና ማቆሚያ፤
- በአንድ ጊዜ እስከ 5,000 ሰዎችን መሰብሰብ የሚያስችል የፕላዛ፣ የአንፊ ቴአትርና የተለያዩ የጥበብ ስራዎችን ማቅረቢያ ስፍራዎችን ይዟል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ " ፕሮጀክቱ የሲቪል ተሳትፎን፣ የባህል ዕድገትን፣ የእግር ጉዞን የሚያበረታታ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በተለይም አቅመ ደካሞችና አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረገ ነው " ብለዋል።
ፕሮጀክቱ ከ500 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች እና ሴቶች የስራ ዕድል መፍጠሩን አመልክተዋል።
#MayorOfficeofAA
@tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ4 ኪሎ ፕላዛን ፣ የ4 ኪሎ የገበያ ማዕከልን እና የመኪና ማቆሚያን በማስመረቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል።
ፕሮጀክቱ ምን ይዟል ?
- ከመሬት በታች የተገነቡ ዘመናዊ የሆኑ 102 የስጦታ እና የአልባሳት መደብሮች፣ ካፌዎች፣ ካፍቴሪያዎች፣ ማንበቢያ ስፍራዎች፣ ሱፐር ማርኬቶች፤
- ከ100 በላይ ተሽከርካሪዎችን በአንድ ጊዜ የሚያስተናግድ የመኪና ማቆሚያ፤
- በአንድ ጊዜ እስከ 5,000 ሰዎችን መሰብሰብ የሚያስችል የፕላዛ፣ የአንፊ ቴአትርና የተለያዩ የጥበብ ስራዎችን ማቅረቢያ ስፍራዎችን ይዟል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ " ፕሮጀክቱ የሲቪል ተሳትፎን፣ የባህል ዕድገትን፣ የእግር ጉዞን የሚያበረታታ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በተለይም አቅመ ደካሞችና አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረገ ነው " ብለዋል።
ፕሮጀክቱ ከ500 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች እና ሴቶች የስራ ዕድል መፍጠሩን አመልክተዋል።
#MayorOfficeofAA
@tikvahethiopia
❤1.34K😡336👏94🙏26🥰20🤔19💔18🕊16😱15😢15😭1