TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ4 ኪሎ ፕላዛን ፣ የ4 ኪሎ የገበያ ማዕከልን እና የመኪና ማቆሚያን በማስመረቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል።

ፕሮጀክቱ ምን ይዟል ?

- ከመሬት በታች የተገነቡ ዘመናዊ የሆኑ 102 የስጦታ እና የአልባሳት መደብሮች፣ ካፌዎች፣ ካፍቴሪያዎች፣ ማንበቢያ ስፍራዎች፣ ሱፐር ማርኬቶች፤

- ከ100 በላይ ተሽከርካሪዎችን በአንድ ጊዜ የሚያስተናግድ የመኪና ማቆሚያ፤

- በአንድ ጊዜ እስከ 5,000 ሰዎችን መሰብሰብ የሚያስችል የፕላዛ፣ የአንፊ ቴአትርና የተለያዩ የጥበብ ስራዎችን ማቅረቢያ ስፍራዎችን ይዟል።

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ " ፕሮጀክቱ የሲቪል ተሳትፎን፣ የባህል ዕድገትን፣ የእግር ጉዞን የሚያበረታታ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በተለይም አቅመ ደካሞችና አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረገ ነው " ብለዋል።

ፕሮጀክቱ ከ500 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች እና ሴቶች የስራ ዕድል መፍጠሩን አመልክተዋል።

#MayorOfficeofAA

@tikvahethiopia
1.34K😡336👏94🙏26🥰20🤔19💔18🕊16😱15😢15😭1