#Tigray 🇪🇹 #EthiopianNationalDialogue
መተማመን እንዲጎለብትና ዘርፈ ብዙ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንዲቻል የፖለቲካ ውይይት ማካሄድ ወሳኝና አስፈላጊ እንደሆነ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን አሳወቀ።
የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀኔራል ) በበኩላቸው የምክክር ኮሚሽኑ ዓላማና ጥረት ለዘላቂ ሰላም ያለውን አወንታዊ አስተዋፅኦ እንደሚገነዘቡ አረጋግጠዋል።
ዛሬ በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ለመጀመሪያ ጊዜ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አመራሮች ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር የፊት ለፊት ግንኙነት አደርገዋል።
የምክክር ኮሚሽኑ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ፣ " አገራዊ ችግሮችና ቁርሾዎቻችን ከንግግርና ውይይት ውጪ ሌላ ፍቱን መድሀኒት የላቸውም " ብለዋል።
" አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ህዝብን የሚያቃቃሩ ትርክቶች ነቅሶ በንግግርና ውይይት በመፍታታ ህዝባዊና አገራዊ መግባባትና መተማመን ፅኑ መሰረት እንዲይዝ አልሞ እየሰራ ነው " ብለዋል።
የአገራዊ የምክክር ኮሚሽኑን ዓላማው አስፈላጊነት በማመን የተናገሩት ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጄነራል) " ከምክክሩ በፊት በፌደራል መንግስትና በትግራይ ክልል መካከል የሚካሄድ የፖለቲካ ውይይት መቅደም አለበት " ብለዋል።
" የትግራይ ህዝብና መንግስት መልሶ ወደ ግጭትና ጦርነት አዙሪት የመግባት ፍላጎት ፈፅሞ የለውም " ያሉት ፕሬዜዳንቱ ፤ የምክክር ኮሚሽኑ በክልሉ ለሚሰራቸው ስራዎች ራሳቸውንና ካቢኔያቸው ተባባሪ ለመሆን ያላቸው ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከፕሬዘዳንት ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
#Peace #Ethiopia
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
መተማመን እንዲጎለብትና ዘርፈ ብዙ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንዲቻል የፖለቲካ ውይይት ማካሄድ ወሳኝና አስፈላጊ እንደሆነ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን አሳወቀ።
የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀኔራል ) በበኩላቸው የምክክር ኮሚሽኑ ዓላማና ጥረት ለዘላቂ ሰላም ያለውን አወንታዊ አስተዋፅኦ እንደሚገነዘቡ አረጋግጠዋል።
ዛሬ በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ለመጀመሪያ ጊዜ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አመራሮች ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር የፊት ለፊት ግንኙነት አደርገዋል።
የምክክር ኮሚሽኑ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ፣ " አገራዊ ችግሮችና ቁርሾዎቻችን ከንግግርና ውይይት ውጪ ሌላ ፍቱን መድሀኒት የላቸውም " ብለዋል።
" አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ህዝብን የሚያቃቃሩ ትርክቶች ነቅሶ በንግግርና ውይይት በመፍታታ ህዝባዊና አገራዊ መግባባትና መተማመን ፅኑ መሰረት እንዲይዝ አልሞ እየሰራ ነው " ብለዋል።
የአገራዊ የምክክር ኮሚሽኑን ዓላማው አስፈላጊነት በማመን የተናገሩት ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጄነራል) " ከምክክሩ በፊት በፌደራል መንግስትና በትግራይ ክልል መካከል የሚካሄድ የፖለቲካ ውይይት መቅደም አለበት " ብለዋል።
" የትግራይ ህዝብና መንግስት መልሶ ወደ ግጭትና ጦርነት አዙሪት የመግባት ፍላጎት ፈፅሞ የለውም " ያሉት ፕሬዜዳንቱ ፤ የምክክር ኮሚሽኑ በክልሉ ለሚሰራቸው ስራዎች ራሳቸውንና ካቢኔያቸው ተባባሪ ለመሆን ያላቸው ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከፕሬዘዳንት ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
#Peace #Ethiopia
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤908🕊159😡49🙏44😭44🤔15😢13🥰9😱1
#Peace🕊
" 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " - አሜሪካ
ከ1980ዎቹ አንስቶ ጦርነት ውስጥ የነበሩት አርሜኒያና አዘርባጃን በአሜሪካ አማካኝነት የሰላም ስምምነት ፈጽመዋል።
የአዘርባጃን ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሌቭ እና የአርሜኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሽኒያን የፈረሙት ስምምነት ለአስርት አመታት የዘለቀውን ግጭት ያስቆማል ተብሏል።
የሰላም ስምምነቱን የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሸማግለዋል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሰላም ስምምነቱን " ረጅም ጊዜ የወሰደ ታሪካዊ ስምምነት ነው " ብለውታል።
ሁለቱ ሀገራት በአወዛጋቢው የናጎርኖ ካራባህ ግዛት ጦርነት ውስጥ እንደነበሩ ያስታወሱት ትራምፕ ግጭቱን " እስከወዲያኛው ይወገዳል " በማለት ተናግረዋል።
ትራምፕ፣ " 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " ብለዋል።
በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ሀገራት የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የንግድ ግንኙነትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲጀመሩ እና ለተፈፃሚነቱ አሜሪካ ጣልቃ እንድትገባ ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
Via @ThiqahEth
" 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " - አሜሪካ
ከ1980ዎቹ አንስቶ ጦርነት ውስጥ የነበሩት አርሜኒያና አዘርባጃን በአሜሪካ አማካኝነት የሰላም ስምምነት ፈጽመዋል።
የአዘርባጃን ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሌቭ እና የአርሜኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሽኒያን የፈረሙት ስምምነት ለአስርት አመታት የዘለቀውን ግጭት ያስቆማል ተብሏል።
የሰላም ስምምነቱን የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሸማግለዋል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሰላም ስምምነቱን " ረጅም ጊዜ የወሰደ ታሪካዊ ስምምነት ነው " ብለውታል።
ሁለቱ ሀገራት በአወዛጋቢው የናጎርኖ ካራባህ ግዛት ጦርነት ውስጥ እንደነበሩ ያስታወሱት ትራምፕ ግጭቱን " እስከወዲያኛው ይወገዳል " በማለት ተናግረዋል።
ትራምፕ፣ " 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " ብለዋል።
በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ሀገራት የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የንግድ ግንኙነትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲጀመሩ እና ለተፈፃሚነቱ አሜሪካ ጣልቃ እንድትገባ ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
Via @ThiqahEth
❤575🕊114👏62🤔26😡9🥰7😱6😢5💔4🙏3