" አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቬትናም የሚያደርገውን የመጀመሪያውን በረራ በዛሬው ዕለት ምሽት ያስጀምራል።
አየር መንገዱ አፍሪካን ከ ኤዥያ ጋር ያገናኘው የዛሬ 52 አመት እ.ኤ.አ በ 1973 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቻይናዋ ከተማ ሻንጋይ በመብረር እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤዢያ 27 መዳረሻዎች ያሉት ሲሆን ወደ ቬትናም ሃኖይ ከተማ የሚያደርገው በረራ 28 ኛው መዳረሻው ይሆናል።
አቶ መስፍን " 190 በረራዎች በሳምንት ወደ ኤዢያ እናደርግ ነበር የአሁኑ በረራ በሳምንት ለ አራት ቀናት የሚከናወን በመሆኑ በአህጉሩ በሳምንት የምናደርገውን በረራ ወደ 194 ከፍ አድርገነዋል " ብለዋል።
ሃኖይ ለንግድ እና ለቱሪዝም የምትመረጥ መዳረሻ በመሆኗም የቀጥታ በረራ በመጀመሩ 120 የሚሆኑ አፍሪካውያን በዛሬው ምሽት ወደ ቬትናም ሃኖይ እንደሚጓዙ ተገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው " አየር መንገዱ በየጊዜው የሚጨምራቸው መዳረሻዎች በምን መስፈርት የተመረጡ ናቸው ? አፍሪካን እርስ በእርስ የማገናኘት ሥራስ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ? " ሲል ጠይቋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው ምን ምላሽ ሰጡ ?
" ወደ አንድ ሃገር እና ከተማ የበረራ መስመር ከመክፈታችን በፊት የአዋጭነት ጥናት እናካሄዳለን።
አዋጭነት ማለት ገበያው አለ ወይ በረራ ብንጀምርስ በቂ መንገደኛ እናገኛለን ወይ የሚለው ላይ ጥናት እናካሂዳለን።
ያ ጥናት በቂ መንገደኛ አለ ሲለን በረራውን እንጀምራለን።
እድገት የሚመጣው አዳዲስ የበረራ መስመሮችን በመጨመር ወይም ባሉት ላይ የበረራ ምልልሱን በመጨመር ነው።
አፍሪካ ውስጥ በአሁኑ ሰአት በ 40 ሃገራት ወደ 61 ከተሞች እንበራለን።
ወደ ፊት እያየን የምንበርባቸው ሃገሮች ተጨማሪ ከተሞችን አዋጭ ሆነው ስናገኛቸው ፈቃዱን እንዳገኘን እንበራለን።
በተጨማሪም የማንበርባቸው ሃገሮችም ፈቃድ እንዳገኘን አዋጭነት እያየን እንበራለን በዚህ መንገድ አፍሪካ ውስጥ መዳረሻችንን እና የበረራ ምልልሱን እንጨምራለን።
አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቬትናም የሚያደርገውን የመጀመሪያውን በረራ በዛሬው ዕለት ምሽት ያስጀምራል።
አየር መንገዱ አፍሪካን ከ ኤዥያ ጋር ያገናኘው የዛሬ 52 አመት እ.ኤ.አ በ 1973 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቻይናዋ ከተማ ሻንጋይ በመብረር እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤዢያ 27 መዳረሻዎች ያሉት ሲሆን ወደ ቬትናም ሃኖይ ከተማ የሚያደርገው በረራ 28 ኛው መዳረሻው ይሆናል።
አቶ መስፍን " 190 በረራዎች በሳምንት ወደ ኤዢያ እናደርግ ነበር የአሁኑ በረራ በሳምንት ለ አራት ቀናት የሚከናወን በመሆኑ በአህጉሩ በሳምንት የምናደርገውን በረራ ወደ 194 ከፍ አድርገነዋል " ብለዋል።
ሃኖይ ለንግድ እና ለቱሪዝም የምትመረጥ መዳረሻ በመሆኗም የቀጥታ በረራ በመጀመሩ 120 የሚሆኑ አፍሪካውያን በዛሬው ምሽት ወደ ቬትናም ሃኖይ እንደሚጓዙ ተገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው " አየር መንገዱ በየጊዜው የሚጨምራቸው መዳረሻዎች በምን መስፈርት የተመረጡ ናቸው ? አፍሪካን እርስ በእርስ የማገናኘት ሥራስ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ? " ሲል ጠይቋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው ምን ምላሽ ሰጡ ?
" ወደ አንድ ሃገር እና ከተማ የበረራ መስመር ከመክፈታችን በፊት የአዋጭነት ጥናት እናካሄዳለን።
አዋጭነት ማለት ገበያው አለ ወይ በረራ ብንጀምርስ በቂ መንገደኛ እናገኛለን ወይ የሚለው ላይ ጥናት እናካሂዳለን።
ያ ጥናት በቂ መንገደኛ አለ ሲለን በረራውን እንጀምራለን።
እድገት የሚመጣው አዳዲስ የበረራ መስመሮችን በመጨመር ወይም ባሉት ላይ የበረራ ምልልሱን በመጨመር ነው።
አፍሪካ ውስጥ በአሁኑ ሰአት በ 40 ሃገራት ወደ 61 ከተሞች እንበራለን።
ወደ ፊት እያየን የምንበርባቸው ሃገሮች ተጨማሪ ከተሞችን አዋጭ ሆነው ስናገኛቸው ፈቃዱን እንዳገኘን እንበራለን።
በተጨማሪም የማንበርባቸው ሃገሮችም ፈቃድ እንዳገኘን አዋጭነት እያየን እንበራለን በዚህ መንገድ አፍሪካ ውስጥ መዳረሻችንን እና የበረራ ምልልሱን እንጨምራለን።
አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tikvahethiopia
❤1.09K👏55🕊21😡16🙏13😭13🥰9🤔9😱1