TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ🇪🇹 የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ፥ " በአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች የሚደረግ ምክክርና እርቀ ሰላም ፍሬው ጣፋጭ ነው " አሉ። ትናንት ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ያቀኑት የትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ዛሬ ሀምሌ 11/2017 ዓ.ም ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) መክረዋል። የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ…
#Peace🕊
የትግራይ ክልል አመራሮችና ፓለቲከኞች አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት የተጀመረውን ሰላም እንዲያፀኑና ከዳር እንዲያደርሱ ተማፅኖ ቀረበ።
ተማፅኖ ያቀረቡት ከ12 ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ናቸው።
ቁጥራቸው 50 የሆኑት መላ የኢትዮጵያ ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የወከሉ የሰላም ልኡካን ዛሬ ሀምሌ 21/2017 ዓ.ም ጠዋት መቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርሱ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የአገር ሽማግሌዎች ፣ ባለሃብቶችና ታዋቂ ሰዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ከአውሮፕላን ማረፍያ ውይይቱ ወደ ሚካሄድበት ቦታ ያቀኑት የሰላም ልኡካኑ ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደና እና ካቢኔያቸው በተገኙበት በየእምነታቸው ፀሎት አድርሰዋል።
የክልሉ አመራሮችና ፓለቲከኞችም ለተሻለ ሰላምና አገራዊ መረጋጋት አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት ተጨማሪ ግጭት እንዲያስቀሩ አባታዊና ሃይማኖታዊ ምክርና ተማፅኖ ቀርበውላቸዋል።
የሰላም ልኡካኑ ከጦርነቱ በፊት ወደ ትግራይ ተመላልሰው ያደረጉት ጥረት ግጭቱ ማስቀረት ባለመቻሉ በቁጭት አስታውሰው ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላ ለሦሥተኛ ጊዜ መምጣታቸውና የሰላም ጥረታቸው ሳይታክቱ እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
" የጀመረው ሰላም እንዲፀና ፤ ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከመስራትና ከመጣር የበለጠ ሃይማኖታዊና አባታዊ ተልእኮ የለንም ለዚህም የሚከፈለውን ሁሉም ዓይነት መስዋእትነት እንከፍላለን " ብለዋል።
የሰላም ልኡካኑ ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርና ካቢኔያቸው ፣ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት፣ የተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ስቪክ ማህበራት እንደሚወያዩ ከወጣው መርሀ ግብር ሐመረዳት ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል አመራሮችና ፓለቲከኞች አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት የተጀመረውን ሰላም እንዲያፀኑና ከዳር እንዲያደርሱ ተማፅኖ ቀረበ።
ተማፅኖ ያቀረቡት ከ12 ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ናቸው።
ቁጥራቸው 50 የሆኑት መላ የኢትዮጵያ ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የወከሉ የሰላም ልኡካን ዛሬ ሀምሌ 21/2017 ዓ.ም ጠዋት መቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርሱ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የአገር ሽማግሌዎች ፣ ባለሃብቶችና ታዋቂ ሰዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ከአውሮፕላን ማረፍያ ውይይቱ ወደ ሚካሄድበት ቦታ ያቀኑት የሰላም ልኡካኑ ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደና እና ካቢኔያቸው በተገኙበት በየእምነታቸው ፀሎት አድርሰዋል።
የክልሉ አመራሮችና ፓለቲከኞችም ለተሻለ ሰላምና አገራዊ መረጋጋት አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት ተጨማሪ ግጭት እንዲያስቀሩ አባታዊና ሃይማኖታዊ ምክርና ተማፅኖ ቀርበውላቸዋል።
የሰላም ልኡካኑ ከጦርነቱ በፊት ወደ ትግራይ ተመላልሰው ያደረጉት ጥረት ግጭቱ ማስቀረት ባለመቻሉ በቁጭት አስታውሰው ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላ ለሦሥተኛ ጊዜ መምጣታቸውና የሰላም ጥረታቸው ሳይታክቱ እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
" የጀመረው ሰላም እንዲፀና ፤ ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከመስራትና ከመጣር የበለጠ ሃይማኖታዊና አባታዊ ተልእኮ የለንም ለዚህም የሚከፈለውን ሁሉም ዓይነት መስዋእትነት እንከፍላለን " ብለዋል።
የሰላም ልኡካኑ ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርና ካቢኔያቸው ፣ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት፣ የተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ስቪክ ማህበራት እንደሚወያዩ ከወጣው መርሀ ግብር ሐመረዳት ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyMekelle
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤625🕊155😡30🤔26🙏24👏7😭4🥰3😱3💔2
#Tigray 🇪🇹 #EthiopianNationalDialogue
መተማመን እንዲጎለብትና ዘርፈ ብዙ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንዲቻል የፖለቲካ ውይይት ማካሄድ ወሳኝና አስፈላጊ እንደሆነ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን አሳወቀ።
የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀኔራል ) በበኩላቸው የምክክር ኮሚሽኑ ዓላማና ጥረት ለዘላቂ ሰላም ያለውን አወንታዊ አስተዋፅኦ እንደሚገነዘቡ አረጋግጠዋል።
ዛሬ በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ለመጀመሪያ ጊዜ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አመራሮች ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር የፊት ለፊት ግንኙነት አደርገዋል።
የምክክር ኮሚሽኑ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ፣ " አገራዊ ችግሮችና ቁርሾዎቻችን ከንግግርና ውይይት ውጪ ሌላ ፍቱን መድሀኒት የላቸውም " ብለዋል።
" አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ህዝብን የሚያቃቃሩ ትርክቶች ነቅሶ በንግግርና ውይይት በመፍታታ ህዝባዊና አገራዊ መግባባትና መተማመን ፅኑ መሰረት እንዲይዝ አልሞ እየሰራ ነው " ብለዋል።
የአገራዊ የምክክር ኮሚሽኑን ዓላማው አስፈላጊነት በማመን የተናገሩት ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጄነራል) " ከምክክሩ በፊት በፌደራል መንግስትና በትግራይ ክልል መካከል የሚካሄድ የፖለቲካ ውይይት መቅደም አለበት " ብለዋል።
" የትግራይ ህዝብና መንግስት መልሶ ወደ ግጭትና ጦርነት አዙሪት የመግባት ፍላጎት ፈፅሞ የለውም " ያሉት ፕሬዜዳንቱ ፤ የምክክር ኮሚሽኑ በክልሉ ለሚሰራቸው ስራዎች ራሳቸውንና ካቢኔያቸው ተባባሪ ለመሆን ያላቸው ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከፕሬዘዳንት ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
#Peace #Ethiopia
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
መተማመን እንዲጎለብትና ዘርፈ ብዙ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንዲቻል የፖለቲካ ውይይት ማካሄድ ወሳኝና አስፈላጊ እንደሆነ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን አሳወቀ።
የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀኔራል ) በበኩላቸው የምክክር ኮሚሽኑ ዓላማና ጥረት ለዘላቂ ሰላም ያለውን አወንታዊ አስተዋፅኦ እንደሚገነዘቡ አረጋግጠዋል።
ዛሬ በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ለመጀመሪያ ጊዜ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አመራሮች ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር የፊት ለፊት ግንኙነት አደርገዋል።
የምክክር ኮሚሽኑ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ፣ " አገራዊ ችግሮችና ቁርሾዎቻችን ከንግግርና ውይይት ውጪ ሌላ ፍቱን መድሀኒት የላቸውም " ብለዋል።
" አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ህዝብን የሚያቃቃሩ ትርክቶች ነቅሶ በንግግርና ውይይት በመፍታታ ህዝባዊና አገራዊ መግባባትና መተማመን ፅኑ መሰረት እንዲይዝ አልሞ እየሰራ ነው " ብለዋል።
የአገራዊ የምክክር ኮሚሽኑን ዓላማው አስፈላጊነት በማመን የተናገሩት ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጄነራል) " ከምክክሩ በፊት በፌደራል መንግስትና በትግራይ ክልል መካከል የሚካሄድ የፖለቲካ ውይይት መቅደም አለበት " ብለዋል።
" የትግራይ ህዝብና መንግስት መልሶ ወደ ግጭትና ጦርነት አዙሪት የመግባት ፍላጎት ፈፅሞ የለውም " ያሉት ፕሬዜዳንቱ ፤ የምክክር ኮሚሽኑ በክልሉ ለሚሰራቸው ስራዎች ራሳቸውንና ካቢኔያቸው ተባባሪ ለመሆን ያላቸው ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከፕሬዘዳንት ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
#Peace #Ethiopia
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤908🕊159😡49🙏44😭44🤔15😢13🥰9😱1
#Peace🕊
" 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " - አሜሪካ
ከ1980ዎቹ አንስቶ ጦርነት ውስጥ የነበሩት አርሜኒያና አዘርባጃን በአሜሪካ አማካኝነት የሰላም ስምምነት ፈጽመዋል።
የአዘርባጃን ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሌቭ እና የአርሜኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሽኒያን የፈረሙት ስምምነት ለአስርት አመታት የዘለቀውን ግጭት ያስቆማል ተብሏል።
የሰላም ስምምነቱን የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሸማግለዋል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሰላም ስምምነቱን " ረጅም ጊዜ የወሰደ ታሪካዊ ስምምነት ነው " ብለውታል።
ሁለቱ ሀገራት በአወዛጋቢው የናጎርኖ ካራባህ ግዛት ጦርነት ውስጥ እንደነበሩ ያስታወሱት ትራምፕ ግጭቱን " እስከወዲያኛው ይወገዳል " በማለት ተናግረዋል።
ትራምፕ፣ " 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " ብለዋል።
በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ሀገራት የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የንግድ ግንኙነትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲጀመሩ እና ለተፈፃሚነቱ አሜሪካ ጣልቃ እንድትገባ ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
Via @ThiqahEth
" 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " - አሜሪካ
ከ1980ዎቹ አንስቶ ጦርነት ውስጥ የነበሩት አርሜኒያና አዘርባጃን በአሜሪካ አማካኝነት የሰላም ስምምነት ፈጽመዋል።
የአዘርባጃን ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሌቭ እና የአርሜኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሽኒያን የፈረሙት ስምምነት ለአስርት አመታት የዘለቀውን ግጭት ያስቆማል ተብሏል።
የሰላም ስምምነቱን የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሸማግለዋል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሰላም ስምምነቱን " ረጅም ጊዜ የወሰደ ታሪካዊ ስምምነት ነው " ብለውታል።
ሁለቱ ሀገራት በአወዛጋቢው የናጎርኖ ካራባህ ግዛት ጦርነት ውስጥ እንደነበሩ ያስታወሱት ትራምፕ ግጭቱን " እስከወዲያኛው ይወገዳል " በማለት ተናግረዋል።
ትራምፕ፣ " 35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል " ብለዋል።
በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ሀገራት የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የንግድ ግንኙነትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲጀመሩ እና ለተፈፃሚነቱ አሜሪካ ጣልቃ እንድትገባ ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
Via @ThiqahEth
❤575🕊113👏62🤔26😡9🥰7😱6😢5💔4🙏3