TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴን ውሳኔ " ተገቢና ህግን ያልተከተለ ውሳኔ " ሲል ተቃወመ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ዋንጫ ከሲዳማ ቡና ተነጥቆ ለወላይታ ዲቻ እንዲመለስ ሲል ውሳኔ አሳልፏል። ይህ ተከትሎ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ውሳኔውን " ተገቢነት የለሌው ውሳኔ ነው። ውሳኔው እጅግ አሳዝኖናል…
" ተክሰናል ፤ ሕዝቡ በልዩ ልዩ መንገዶች ደስታዉን እየገለፀ ነዉ " - የወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ

ዛሬ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ያስተላለፈዉን ዉሳኔ ተከትሎ የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ " የኢትዮጵያ ዋንጫን " ለወላይታ ዲቻ ይመልሳል ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ቡድንም በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ #ኢትዮጵያን የሚወክል ይሆናል።

ይህን የፌደሬሽኑን ዉሳኔ ተከትሎ የወላይታ ዲቻ ደጋፊዎች በአደባባይ ደስታቸዉን የገለፁ ሲሆን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላላ ከበደን ጨምሮ የክልሉና የወላይታ ዞን አመራሮች " የእንኳን ደስ ያላችሁ " መልዕክት አስተላልፈዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገርናቸው የወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ሆሲሶ " ዉሳኔዉ በእግር ኳሱ ዘርፍ ተስፋ ሰጪና ለወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ቡድን ደጋፊዎች ትልቅ ደስታን የፈጠረ ተገቢ ዉሳኔ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ተክሰናል " ያሉት ስራ አስኪያጁ " የዉሳኔዉን አፈጻጸም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በሚያስቀሚጠዉ ዕቅድ መሰረት ተፈፃሚ እናደርጋለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
1.53K😱173😡143🤔78👏56😭39🕊33🙏28🥰27💔11😢5