#ለጥንቃቄ
" ' አሟታል ' ፣ ' ነፍሰ ጡር ናት ' ፣ ' መስኮት ክፈት ' ፣ ' ተባበራት ' ፣ ' ትራፊክ መጣ ዝቅ በል ' በማለት በማዋከብ ' ከታክሲው ውረጂ/ ውረድ ' ሌላም ምክንያቶችን በመናገር ገፍትረው የሚያመልጡ ስለሆነ ጥንቃቄ አድርጉ ! " -ፖሊስ
የአዲስ አበባ ፖሊስ CMC አካባቢ የማታለል (#ሿሿ) ወንጀል ላይ የተሰማሩ 9 ተጠርጣሪዎችን በተበዳይ ጥቆማ መያዙን አሳውቋል።
እነዚህ ግለሰቦች የግል ተበዳይን " የት ነህ ? " በማለት ከCMC ጋስትሞል ይጭናሉ።
የተወሰነ ርቀት እንደተጓዙ CMC የጋራ መኖሪያ ቤቶች (5 መቶ አፖርታማ) ጋር ሲደርሱ ግን " ትራፊክ አለ ውረድ " ብለው የተሽከርካሪውን በር ከፍተው ገፍትረው ጥለው ይሰወራሉ።
የግል ተበዳይም ጉዳዩን ለCMC አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ማመልከታቸውን ተከትሎ ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን ወማደን ይገባል።
በዚህም በአራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ አካባቢ ሹፌርና ረዳት እንዲሁም ተሳፋሪ በመምሰል ወንጀሉን የሚፈፅሙ 9 ተጠርጣሪዎችን ለወንጀል መፈጸሚያ ከሚገለገሉበት የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 ኦ/ሮ 78652 ተሽከርካሪ ጋር መያዙን ፖሊስ ገልጿል።
በግለሰቦቹ ላይ አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብ ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን አሳውቋል።
ተመሳሳይ የማታለል ወይም የሿሿ ወንጀል የተፈፀመበት ማንኛውም ግለሰብ CMC አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቀርቦ ወንጀል ፈፃሚዎቹን በመለየትና በመምረጥ ማስረጃ መስጠት የሚችል መሆኑ ተገልጿል።
የሿሿ የወንጀል ተግባር ላይ የተሰማሩ ሰዎች በተሽከርካሪዎቻቸው ውስጥ ወንድና ሴት በመጫን ፦
- " አሟታል "
- " ነፍሰ ጡር ናት "
- " መስኮት ክፈት "
- " ተባበራት "
- " ትራፊክ መጣ ዝቅ በል " በማለት በማዋከብ " ከታክሲው ውረድ " ሌላም ምክንያቶችን በመናገር ገፍትረው የሚያመልጡ በመሆኑ ህብረተሰቡ ለወንጀል ፈፃሚዎች ሰለባ ላለመሆን ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ፖሊስ አሳስቧል።
የወንጀል ድርጊቱ ከተፈፀመበትም የሰሌዳ ቁጥር የመያዝ ልምዱን ሊያጎለብት እንደሚገባ አስገንዘቧል።
⚠️ ትራንስፖርት ስትጠቀሙ የምትጠቀሙበትን ተሽከርካሪ ታርጋ ቁጥር መያዝ እንዳትዘነጉ።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
" ' አሟታል ' ፣ ' ነፍሰ ጡር ናት ' ፣ ' መስኮት ክፈት ' ፣ ' ተባበራት ' ፣ ' ትራፊክ መጣ ዝቅ በል ' በማለት በማዋከብ ' ከታክሲው ውረጂ/ ውረድ ' ሌላም ምክንያቶችን በመናገር ገፍትረው የሚያመልጡ ስለሆነ ጥንቃቄ አድርጉ ! " -ፖሊስ
የአዲስ አበባ ፖሊስ CMC አካባቢ የማታለል (#ሿሿ) ወንጀል ላይ የተሰማሩ 9 ተጠርጣሪዎችን በተበዳይ ጥቆማ መያዙን አሳውቋል።
እነዚህ ግለሰቦች የግል ተበዳይን " የት ነህ ? " በማለት ከCMC ጋስትሞል ይጭናሉ።
የተወሰነ ርቀት እንደተጓዙ CMC የጋራ መኖሪያ ቤቶች (5 መቶ አፖርታማ) ጋር ሲደርሱ ግን " ትራፊክ አለ ውረድ " ብለው የተሽከርካሪውን በር ከፍተው ገፍትረው ጥለው ይሰወራሉ።
የግል ተበዳይም ጉዳዩን ለCMC አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ማመልከታቸውን ተከትሎ ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን ወማደን ይገባል።
በዚህም በአራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ አካባቢ ሹፌርና ረዳት እንዲሁም ተሳፋሪ በመምሰል ወንጀሉን የሚፈፅሙ 9 ተጠርጣሪዎችን ለወንጀል መፈጸሚያ ከሚገለገሉበት የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 ኦ/ሮ 78652 ተሽከርካሪ ጋር መያዙን ፖሊስ ገልጿል።
በግለሰቦቹ ላይ አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብ ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን አሳውቋል።
ተመሳሳይ የማታለል ወይም የሿሿ ወንጀል የተፈፀመበት ማንኛውም ግለሰብ CMC አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቀርቦ ወንጀል ፈፃሚዎቹን በመለየትና በመምረጥ ማስረጃ መስጠት የሚችል መሆኑ ተገልጿል።
የሿሿ የወንጀል ተግባር ላይ የተሰማሩ ሰዎች በተሽከርካሪዎቻቸው ውስጥ ወንድና ሴት በመጫን ፦
- " አሟታል "
- " ነፍሰ ጡር ናት "
- " መስኮት ክፈት "
- " ተባበራት "
- " ትራፊክ መጣ ዝቅ በል " በማለት በማዋከብ " ከታክሲው ውረድ " ሌላም ምክንያቶችን በመናገር ገፍትረው የሚያመልጡ በመሆኑ ህብረተሰቡ ለወንጀል ፈፃሚዎች ሰለባ ላለመሆን ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ፖሊስ አሳስቧል።
የወንጀል ድርጊቱ ከተፈፀመበትም የሰሌዳ ቁጥር የመያዝ ልምዱን ሊያጎለብት እንደሚገባ አስገንዘቧል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.11K🙏144👏59🤔24😢14😭11🕊8😱1