TIKVAH-ETHIOPIA
አዋጅ ቁጥር 1387/2017 በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረት ወይም ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብንና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የወጣው አዋጅ ቁጥር 780/2005 ‘ን ለማሻሻል የወጣው ሰሞኑም የፀደቀውን አዋጅ ቁጥር 1387/2017ን በተመለከተ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ምን አለ ? " ኢትዮጵያ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረትን ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ እና ሽብርተኝነትን…
#UndercoverInvestigation
" ከፍርድ ቤት ፍቃድ ውጪ የሚደረግ ምርመራን አዋጁ አይፈቅድም " - የፍትሕ ሚኒስቴር
የፍትሕ ሚኒስቴር ፤ በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ከፍርድ ቤት ፍቃድ ውጪ የሚደረግ ምርመራን እንደማይፈቅድ አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ ሰሞኑን በፓላማው የፀደቀውን የተሻሻለ አዋጅ በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።
በዚህም " አዋጁን አንዳንዶች የተረዱበት መንገድ ልክ አይደለም " ብሏል፡፡
የፍትሕ ሚኒስቴር ምን አለ ?
" አዲሱ አዋጅ ከመደበኛ የወንጀል መርመራ ሂደት የወጣ መንገድን የሚከተል እንደሆነ ሰው ሊረዳው ይገባል።
አዲሱ አዋጅ ልክ በመደበኛው የምርመራ ሂደት እንደሚደረገው ተጠርጣሪዎችን በፍርድ ቤት መያዣ መያዝ ፣ ሰነዶችን ማሰባሰብ፣ ምስከሮችን መስማት እና መሰል ሂደቶችን አይከተልም።
አዋጁ ወስብስብ የሆኑ ወንጀሎችን ከመሰረቱ ለመለየት የሚስችል የምርመራ ሂደትን የሚከተል ነው።
ለምሳሌም፦ መርማሪው አካል ወንጀለኞችን መስሎ ተቀላቅሎ ወይንም አብሮ በመስራት፣ ተባባሪ መስሎ አብሮ ውሎ በማደር፣ ሲሸጡ ገዢ መስሎ ፣ ሲገዙ ሻጭ መስሎ ሊሆን ይችላል።
ምርመራውን የሚየካሂደው አካል ምረመራ ማድረግ የሚችለው የፍርድ ቤት ተዕዛዝ ካገኘ ብቻ ነው።
ፍርድ ቤት በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራ ተግባራዊ እንዲደረግ በአሳማኝ ምክንያት ሲፈቅድ ምርመራው የሚፈጸምበትን ዘዴ ፣ የአተገባበር ሁኔታ ፣ የሚከናወንበትን ጊዜ በትዕዛዙ ላይ በግልጽ ማስቀመጥ እንዳለበት አዋጁ ደንግጓል።
እንደሚባለው አዋጁ ተጠርጣሪን አስሮ እያሰቃዩ አይመረምርም ይህም ፍጹም ስህተት ነው። በማስገደድ ማስረጃ የሚሰበሰብበትም አይደለም።
መርማሪው ፍርድ ቤት አሳማኝ ምክንያት ሲፈቅድለት በሽፋን ስር የሚደረግ ልዩ የምርመራ ዘዴን ይተገብራል ሲባል በተጠርጣሪዎች ወይም በሌላ ሦስተኛ ወገኖች ላይ ወንጀል ሊፈጽምባቸው ይችላል፤ ወንጀሉን ከፈጸመባቸው በኋላ በወንጀል አይጠየቅም የሚል አይደለም።
ከተጠርጣሪዎች ጋር የወንጀል ተካፋይ ወይም ግብረ-አበር በመሆን በራሱ ፈቃድ አስቦና ፈቅዶ ሳይሆን ፦
- ያለፈቃዱ፣
- ተገዶ፣
- በተጽእኖ፣
- በተጠርጣሪዎች ሕገ ወጥ ትዕዛዝ ወይም ከአቅሙ በላይ በሆነ ማንኛውንም ምክንያት ሌላ ከባድ ጉዳትን ለማስቀረት ወይም የተሰጠውን ሕጋዊ ተልእኮ ለማሳካት ሲል ወንጀል የሚፈጽምበት ሁኔታ ሲኖር ከወንጀል ክስ #ነጻ የሚደረግበትን ሁኔታ ለማመላከት የተደነገገ ድንጋጌ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። " ብሏል።
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን የሚመረምር ሰው፤ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት ከግድያ ውጪ የትኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢፈጽም ተጠያቂ የማያደርግ አዋጅ ከሰሞኑ መፅደቁ ይታወሳል፡፡
ይህም መርማሪዎችን ወንጀል እንዲፈፅሙ በር ይከፍታል በሚል ከምክር ቤት ትችት ሲቀርብበት ነበር።
#MinistryofJustice #FinancialIntelligenceService #ShegerFM
@tikvahethiopia
" ከፍርድ ቤት ፍቃድ ውጪ የሚደረግ ምርመራን አዋጁ አይፈቅድም " - የፍትሕ ሚኒስቴር
የፍትሕ ሚኒስቴር ፤ በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ከፍርድ ቤት ፍቃድ ውጪ የሚደረግ ምርመራን እንደማይፈቅድ አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ ሰሞኑን በፓላማው የፀደቀውን የተሻሻለ አዋጅ በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።
በዚህም " አዋጁን አንዳንዶች የተረዱበት መንገድ ልክ አይደለም " ብሏል፡፡
የፍትሕ ሚኒስቴር ምን አለ ?
" አዲሱ አዋጅ ከመደበኛ የወንጀል መርመራ ሂደት የወጣ መንገድን የሚከተል እንደሆነ ሰው ሊረዳው ይገባል።
አዲሱ አዋጅ ልክ በመደበኛው የምርመራ ሂደት እንደሚደረገው ተጠርጣሪዎችን በፍርድ ቤት መያዣ መያዝ ፣ ሰነዶችን ማሰባሰብ፣ ምስከሮችን መስማት እና መሰል ሂደቶችን አይከተልም።
አዋጁ ወስብስብ የሆኑ ወንጀሎችን ከመሰረቱ ለመለየት የሚስችል የምርመራ ሂደትን የሚከተል ነው።
ለምሳሌም፦ መርማሪው አካል ወንጀለኞችን መስሎ ተቀላቅሎ ወይንም አብሮ በመስራት፣ ተባባሪ መስሎ አብሮ ውሎ በማደር፣ ሲሸጡ ገዢ መስሎ ፣ ሲገዙ ሻጭ መስሎ ሊሆን ይችላል።
ምርመራውን የሚየካሂደው አካል ምረመራ ማድረግ የሚችለው የፍርድ ቤት ተዕዛዝ ካገኘ ብቻ ነው።
ፍርድ ቤት በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራ ተግባራዊ እንዲደረግ በአሳማኝ ምክንያት ሲፈቅድ ምርመራው የሚፈጸምበትን ዘዴ ፣ የአተገባበር ሁኔታ ፣ የሚከናወንበትን ጊዜ በትዕዛዙ ላይ በግልጽ ማስቀመጥ እንዳለበት አዋጁ ደንግጓል።
እንደሚባለው አዋጁ ተጠርጣሪን አስሮ እያሰቃዩ አይመረምርም ይህም ፍጹም ስህተት ነው። በማስገደድ ማስረጃ የሚሰበሰብበትም አይደለም።
መርማሪው ፍርድ ቤት አሳማኝ ምክንያት ሲፈቅድለት በሽፋን ስር የሚደረግ ልዩ የምርመራ ዘዴን ይተገብራል ሲባል በተጠርጣሪዎች ወይም በሌላ ሦስተኛ ወገኖች ላይ ወንጀል ሊፈጽምባቸው ይችላል፤ ወንጀሉን ከፈጸመባቸው በኋላ በወንጀል አይጠየቅም የሚል አይደለም።
ከተጠርጣሪዎች ጋር የወንጀል ተካፋይ ወይም ግብረ-አበር በመሆን በራሱ ፈቃድ አስቦና ፈቅዶ ሳይሆን ፦
- ያለፈቃዱ፣
- ተገዶ፣
- በተጽእኖ፣
- በተጠርጣሪዎች ሕገ ወጥ ትዕዛዝ ወይም ከአቅሙ በላይ በሆነ ማንኛውንም ምክንያት ሌላ ከባድ ጉዳትን ለማስቀረት ወይም የተሰጠውን ሕጋዊ ተልእኮ ለማሳካት ሲል ወንጀል የሚፈጽምበት ሁኔታ ሲኖር ከወንጀል ክስ #ነጻ የሚደረግበትን ሁኔታ ለማመላከት የተደነገገ ድንጋጌ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። " ብሏል።
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን የሚመረምር ሰው፤ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት ከግድያ ውጪ የትኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢፈጽም ተጠያቂ የማያደርግ አዋጅ ከሰሞኑ መፅደቁ ይታወሳል፡፡
ይህም መርማሪዎችን ወንጀል እንዲፈፅሙ በር ይከፍታል በሚል ከምክር ቤት ትችት ሲቀርብበት ነበር።
#MinistryofJustice #FinancialIntelligenceService #ShegerFM
@tikvahethiopia
❤1.16K😡270🙏62🤔51😭31😢20🕊20💔19👏17😱4🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia🇪🇹 የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ እንደሚሻሻል ተገልጿል። ዛሬ 48ኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ተካሂዶ የአዋጁ መሻሻል ላይ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ " ቀደም ሲል ሲሰራበት የነበረው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ አሁን ከምንገኝበት ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ሲታይ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት ነው " ብሏል። " የአዋጁን ድንጋጌዎች በማሻሻል የታክስ ስርአቱ…
#Ethiopia🇪🇹
" አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም ! " - የምክር ቤት አባል
በገቢ ግብር ማሻሽያ አዋጅ ላይ ዝቅተኛ የግብር ከፋይ መነሻ ደመወዝ 5,000 ብር እንዲሆን በምክር ቤት ተጠየቀ፡፡
ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዛሬ ከሰዓት በጠራው ልዩ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡
አሁን በስራ ላይ ያለው የገቢ ግብር አዋጅ ከዘመኑ የኢኮኖሚ ሁኔታ አብሮ እንደማይሄድ እና ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር እንደማይጣጣም በአዋጁ ላይ በቀረበው አጭር ማብራርያ ተመላክቷል፡፡
የማሻሽያ አዋጁን በተመለከተ ሃሳብ የሰጡት የምክርቤት አባሉ አቶ ባርጠማ ፍቃዱ ምን አሉ ?
- በአዋጁ አንቅጽ 11 ላይ የቀድሞው ተሰርዞ አዲስ ሃሳብ ገብቷል። ከዚህ በፊት ተቀጣሪ ከደሞዘ የሚከፍለው ግብር ከ600 ብር በላይ ጀምሮ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው አዋጅ ግን ከ600 ብር ወደ 2,000 ብር አድጓል።
- በመሰረቱ 2 ሺ ብር አሁን በአገራችን የሚቀጠር ሰው የለም።
- ከዚህ ቀደም በመንግስት ተቋም ጽዳት ፣የጉልበት ስራ እና የመሳሰሉ ስራዎች ነበሩ ከ600 ብር እስከ 1,000 ብር ደሞዝ አሁን ባለው ሁኔታ ከ4,500 ብር በላይ ነው ቅጥር ያለው።
- አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም።
- ቢያንስ እንኳን ዝቅተኛ ተቀጣሪው ከግብር ነጻ ቢሆን ጥሩ ነው።
- ግብር ከፋይዉም ከ5,000 በላይ ያለው ስራተኛ ቢሆን።
- የ35 በመቶ ግብር እንዲከፍል የተቀመጠው ከ14ሺ 100 በላይ ነው። ይህም ከወቅቱ ገበያ አንጻር ሲታይ ምንም ነው፤ በዚህ ላይ 35 በመቶ ግብር ሲቆረጥበት ደግሞ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ ወደ 20 ሺ በላይ ከፍ ቢል።
- በስራ ላይ ባለው አዋጅ #መነሻ_ግብር 10 በመቶ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው ረቂቅ አዋጁ ግን 15 በመቶ ብሎ ነው የሚጀምረው ይህም ወደ ቀድሞው ወደ 10 በመቶ ቢመለስ ሲሉ ጥሩ ነው።
የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን በስራ ላይ ባለው አዋጅ ላይ ያለው ከፍተኛ ግብር የሚከፈልበት ደሞዝ በተሸሻለው አዋጅ የዝቅተኛ ግብር መነሻ እንዲሆን መጠየቁ ይታወሳል።
ኮንፌደሬሽኑ የሰራተኛውን ኑሮ ያገናዘበ የገቢ ግብር ማሻሽያ እንዲደረግም ጠይቆ ነበር፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህበረተሰብ ክፍል ፦
- የሚያርፍበትን የግብር ጫና መቀነስ፤
- የግብር መሰረትን ማስፋት፤
- የግብር ስርአቱ ላይ የሚታዩ የፍትሃዊነት ችግሮችን መቅረፍ፤
- የአነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች የግብር አከፋፈል ስርአት ቀላል እንዲሆን ማድረግ፤
- ከአዋጁ አላማዎች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡
ም/ቤቱ እነዚህን እና ሌሎች ከአባላት የተነሱ ሃሳቦች ታክለውበት ረቂቅ አዋጁ ለፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳይዎች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቶታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
" አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም ! " - የምክር ቤት አባል
በገቢ ግብር ማሻሽያ አዋጅ ላይ ዝቅተኛ የግብር ከፋይ መነሻ ደመወዝ 5,000 ብር እንዲሆን በምክር ቤት ተጠየቀ፡፡
ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዛሬ ከሰዓት በጠራው ልዩ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡
አሁን በስራ ላይ ያለው የገቢ ግብር አዋጅ ከዘመኑ የኢኮኖሚ ሁኔታ አብሮ እንደማይሄድ እና ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር እንደማይጣጣም በአዋጁ ላይ በቀረበው አጭር ማብራርያ ተመላክቷል፡፡
የማሻሽያ አዋጁን በተመለከተ ሃሳብ የሰጡት የምክርቤት አባሉ አቶ ባርጠማ ፍቃዱ ምን አሉ ?
- በአዋጁ አንቅጽ 11 ላይ የቀድሞው ተሰርዞ አዲስ ሃሳብ ገብቷል። ከዚህ በፊት ተቀጣሪ ከደሞዘ የሚከፍለው ግብር ከ600 ብር በላይ ጀምሮ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው አዋጅ ግን ከ600 ብር ወደ 2,000 ብር አድጓል።
- በመሰረቱ 2 ሺ ብር አሁን በአገራችን የሚቀጠር ሰው የለም።
- ከዚህ ቀደም በመንግስት ተቋም ጽዳት ፣የጉልበት ስራ እና የመሳሰሉ ስራዎች ነበሩ ከ600 ብር እስከ 1,000 ብር ደሞዝ አሁን ባለው ሁኔታ ከ4,500 ብር በላይ ነው ቅጥር ያለው።
- አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም።
- ቢያንስ እንኳን ዝቅተኛ ተቀጣሪው ከግብር ነጻ ቢሆን ጥሩ ነው።
- ግብር ከፋይዉም ከ5,000 በላይ ያለው ስራተኛ ቢሆን።
- የ35 በመቶ ግብር እንዲከፍል የተቀመጠው ከ14ሺ 100 በላይ ነው። ይህም ከወቅቱ ገበያ አንጻር ሲታይ ምንም ነው፤ በዚህ ላይ 35 በመቶ ግብር ሲቆረጥበት ደግሞ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ ወደ 20 ሺ በላይ ከፍ ቢል።
- በስራ ላይ ባለው አዋጅ #መነሻ_ግብር 10 በመቶ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው ረቂቅ አዋጁ ግን 15 በመቶ ብሎ ነው የሚጀምረው ይህም ወደ ቀድሞው ወደ 10 በመቶ ቢመለስ ሲሉ ጥሩ ነው።
የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን በስራ ላይ ባለው አዋጅ ላይ ያለው ከፍተኛ ግብር የሚከፈልበት ደሞዝ በተሸሻለው አዋጅ የዝቅተኛ ግብር መነሻ እንዲሆን መጠየቁ ይታወሳል።
ኮንፌደሬሽኑ የሰራተኛውን ኑሮ ያገናዘበ የገቢ ግብር ማሻሽያ እንዲደረግም ጠይቆ ነበር፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህበረተሰብ ክፍል ፦
- የሚያርፍበትን የግብር ጫና መቀነስ፤
- የግብር መሰረትን ማስፋት፤
- የግብር ስርአቱ ላይ የሚታዩ የፍትሃዊነት ችግሮችን መቅረፍ፤
- የአነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች የግብር አከፋፈል ስርአት ቀላል እንዲሆን ማድረግ፤
- ከአዋጁ አላማዎች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡
ም/ቤቱ እነዚህን እና ሌሎች ከአባላት የተነሱ ሃሳቦች ታክለውበት ረቂቅ አዋጁ ለፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳይዎች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቶታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.85K👏245🙏64😡60😢43🕊23😭22🤔20😱19🥰7