" ህክምናውን ለማግኘት በተስፋ ሲጠባበቁ ለነበሩ 88 ህፃናት ህክምና መስጠት ተችሏል " - የኢትዮጲያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ
የኢትዮጲያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ በ6 ቀናት ለ88 የልብ ሕሙማን ሕፃናት የልብ ሕክምና መስጠቱን ገልጿል።
ከኪንግ ሰልማንሁማኒተሪያን ኤይድ ኤንድ ሪሊፍሴንተር ( KSrelief) በተሰጠው በዚህ የህክምና ተልዕኮ ከማዕከሉ የመጡ 30 የህክምና ባለሙያዎች ከማዕከሉ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የህክምና ቡድኑ ከማዕከሉ ባለሞያዎቾ ጋር በመተባበር ፦
- ለ24 ህፃናት የልብ ቀዶ ህክምና፤
- ለ64 ህፃናት ደግሞ በደም ስር በኩል የሚሰጥ የልብ ህክምና ወይም (cathertarazation) ህክምና መስጠት ችሏል።
በዚህም፥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ለነበሩ እና ህክምናውን ለማግኘት በተስፋ ሲጠባበቁ የነበሩ አጠቃላይ 88 ህፃናት ህክምና ማግኘት ችለዋል።
ሳልማን ሁማኒተሪያን ኤይድ ኤንድ ሪሊፍ ሴንተር የህክምና ቡድን የፈፀመው የህክምና አገልግሎት በብር ሲተመን ከ39 አስከ 51 ሚልየን የሚገመት እንደሆነ የኢትዮጲያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ጠቅሷል።
ተቋሙ ከሳኡዲ አረቢያድረስ በመምጣት ላበረከተው ትልቅ ኣስተዋፅኦም ምስጋና ያቀረበ ሲሆን አጋርነታቸውን በማስቀጠል በልብ ሕመም ከሚሰቃዩ ሕፃናት ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
የኢትዮጲያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ በ6 ቀናት ለ88 የልብ ሕሙማን ሕፃናት የልብ ሕክምና መስጠቱን ገልጿል።
ከኪንግ ሰልማንሁማኒተሪያን ኤይድ ኤንድ ሪሊፍሴንተር ( KSrelief) በተሰጠው በዚህ የህክምና ተልዕኮ ከማዕከሉ የመጡ 30 የህክምና ባለሙያዎች ከማዕከሉ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የህክምና ቡድኑ ከማዕከሉ ባለሞያዎቾ ጋር በመተባበር ፦
- ለ24 ህፃናት የልብ ቀዶ ህክምና፤
- ለ64 ህፃናት ደግሞ በደም ስር በኩል የሚሰጥ የልብ ህክምና ወይም (cathertarazation) ህክምና መስጠት ችሏል።
በዚህም፥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ለነበሩ እና ህክምናውን ለማግኘት በተስፋ ሲጠባበቁ የነበሩ አጠቃላይ 88 ህፃናት ህክምና ማግኘት ችለዋል።
ሳልማን ሁማኒተሪያን ኤይድ ኤንድ ሪሊፍ ሴንተር የህክምና ቡድን የፈፀመው የህክምና አገልግሎት በብር ሲተመን ከ39 አስከ 51 ሚልየን የሚገመት እንደሆነ የኢትዮጲያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ጠቅሷል።
ተቋሙ ከሳኡዲ አረቢያድረስ በመምጣት ላበረከተው ትልቅ ኣስተዋፅኦም ምስጋና ያቀረበ ሲሆን አጋርነታቸውን በማስቀጠል በልብ ሕመም ከሚሰቃዩ ሕፃናት ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
❤1.91K👏197🙏137😡28🥰18🕊11😱7😭7🤔4😢3💔3