TIKVAH-ETHIOPIA
" የቤተክርስቲያን ማሳ እያረሱ በነበሩ ሰዎች ላይ ጥቃት ተፈፅሞ የአንድ አርሶ አደር ሕይወት ጠፍቷል " - የኮሬ ዞን ጎርካ ነዋሪዎች እና የሃይማኖት አባቶች ባሳለፍነዉ ቅዳሜ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ " ጃሎ " ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በታጠቁ ሃይሎች በተፈፀመ ጥቃት የሁለት ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን ይታወቃል። ዛሬ ከቀኑ 7 ሰዓት ገደማ በወረዳዉ " ዳኖ ቡልቶ " ተብሎ በሚጠራው አከባቢ…
" ከኬሌ - ዲላ መንገድ ለጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት ይደረጋል፤ መንገዱ ክፍት የሚደረገው ግን የፀጥታ መዋቅር በሚያስቀምጠው የሰዓት ገደብ ነው " - አቶ ወገኔ ብዙነህ
በደቡብ ኢትዮጵያ እና ኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አዋሳኝ አካባቢዎች የሚታየውን የሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ያለ የፀጥታ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ የምክክር መድረክ መካሄዱ ተሰምቷል።
በምክክር መድረኩ ህዝብ መካከል ያሉ የተደራጁ ንብረት ዘራፊዎች እና ነፍስ አጥፊዎች ላይ የህግ የበላይነት ማስከበር እንዲሁም ሀገር መከላከያ ሠራዊት ኦፕሬሽን አድርጎ አካባቢውን ለማፅዳት የሚሰራውን ስራ ማገዝ ከዛ ባለፈ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እዲጠናከርና ሰላም እንዲፀና መስራት ይገባል ተብሏል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች እነማን ነበሩ ?
- የሀገር መከላከያ ሰራዊት
- የኮሬ ዞን
- የቡርጂ ዞን
- የምዕራብ ጉጂ ዞን
- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ
ምን ተባለ ?
የኮሬ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ፤ መድረኩ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለመጀመር ወሳኝ እና ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።
በኮሬ ዞን በኩል እየተሰራ ባለ የህግ የበላይነትን የማስከበር ስራ የፀጥታው ሁኔታ እየተረጋጋ መምጣቱን ጠቁመዋል።
የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኣቶ ዳኜ ሂዶ ፤ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር ሁሉ። መዋቅሮች ኃላፊነት መውሰድ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የምዕራብ ጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዱላ ህርባዬ ፤ መድረኩ አላማው የተሳሳቱ አመለካከቶችን ማስተካከል ጥርጣሬ በማስወገድ ግልፀኝነት መፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል።
በቀጣይ የቀበሌ እና የወረዳ አመራሮች የእርስ በእርስ ግንኙነት በማጠናከር ቅንጅታዊ ኦፕሬሽን ማድረግ፣ ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማጠናከር ላይ ይሰራል ብለዋል።
ሶስቱም ዞኖች በጋራ ሆነው የቆመው የፍስሃ ገነት - ኬሌ - ነዳሌ የአስፋልት መንገድ እንዲጀመር መጠየቅ ያስፈልጋል ብለዋል።
የሀገር መከላከያ ሠራዊት 37ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ካሳዬ ተገኝ ፤ ቀጠናው ዘላቂ ሰላም እንዲያገኝ ከቀበሌ አንስቶ የህዝብ አመለካከት ላይ ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ህዝቡ ወንጀለኞችን ለህግ አሳልፎ እንዲሰጥ ማድረግ ፣ ፀረሰላም ኃይሎች የሚንቀሳሰቁባቸውን ቀበሌያት ወሰን አካባቢ ህዝባዊ ሰራዊት እና ሚሊሻ ማደራጀት እንደሚገባ ገልጸዋል።
በሰላም ግንባታ ላይ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሚናቸውን እንዲጫወቱ ጠይቀዋል።
መከላከያ ለሚሰራው ኦፕሬሽን አዋሳኝ ቀበሌያት ያለው ህዝብ እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ ፥ " የተጀመረውን የአመራር ለአመራር እርስ በእርስ ግንኙነት ለማደናቀፍ የሚሰራ ፀረ ሰላም አለ " ብለዋል።
በመሆኑን የፀጥታ መዋቅሩ በተጠንቀቅ መቆም አለበት ሲሉ አስገንዝበዋል።
ሁለቱም መዋቅር አመራርና ፀጥታ አካላት እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሠራዊት በጋራ ተስማምተው በሚያስቀምጡት የሰዓት ገደብ መሰረት ከኬሌ - ዲላ መንገድ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ገልጸዋል።
" ከዛሬ ጀምሮ በቀጠናው የሰው ነፍስ የሚያጠፉ ንብረት የሚዘርፉ በኮሬ፣ ቡርኪና ጉጂ ስም የሚነግዱ ህገወጦች ወደ ቤት ግቡ " ሲሉ አሳስበዋል።
#KooreZone #BurjiZone #WestGujii #FDREDefenseForce
@tikvahethiopia
በደቡብ ኢትዮጵያ እና ኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አዋሳኝ አካባቢዎች የሚታየውን የሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ያለ የፀጥታ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ የምክክር መድረክ መካሄዱ ተሰምቷል።
በምክክር መድረኩ ህዝብ መካከል ያሉ የተደራጁ ንብረት ዘራፊዎች እና ነፍስ አጥፊዎች ላይ የህግ የበላይነት ማስከበር እንዲሁም ሀገር መከላከያ ሠራዊት ኦፕሬሽን አድርጎ አካባቢውን ለማፅዳት የሚሰራውን ስራ ማገዝ ከዛ ባለፈ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እዲጠናከርና ሰላም እንዲፀና መስራት ይገባል ተብሏል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች እነማን ነበሩ ?
- የሀገር መከላከያ ሰራዊት
- የኮሬ ዞን
- የቡርጂ ዞን
- የምዕራብ ጉጂ ዞን
- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ
ምን ተባለ ?
የኮሬ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ፤ መድረኩ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለመጀመር ወሳኝ እና ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።
በኮሬ ዞን በኩል እየተሰራ ባለ የህግ የበላይነትን የማስከበር ስራ የፀጥታው ሁኔታ እየተረጋጋ መምጣቱን ጠቁመዋል።
የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኣቶ ዳኜ ሂዶ ፤ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር ሁሉ። መዋቅሮች ኃላፊነት መውሰድ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የምዕራብ ጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዱላ ህርባዬ ፤ መድረኩ አላማው የተሳሳቱ አመለካከቶችን ማስተካከል ጥርጣሬ በማስወገድ ግልፀኝነት መፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል።
በቀጣይ የቀበሌ እና የወረዳ አመራሮች የእርስ በእርስ ግንኙነት በማጠናከር ቅንጅታዊ ኦፕሬሽን ማድረግ፣ ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማጠናከር ላይ ይሰራል ብለዋል።
ሶስቱም ዞኖች በጋራ ሆነው የቆመው የፍስሃ ገነት - ኬሌ - ነዳሌ የአስፋልት መንገድ እንዲጀመር መጠየቅ ያስፈልጋል ብለዋል።
የሀገር መከላከያ ሠራዊት 37ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ካሳዬ ተገኝ ፤ ቀጠናው ዘላቂ ሰላም እንዲያገኝ ከቀበሌ አንስቶ የህዝብ አመለካከት ላይ ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ህዝቡ ወንጀለኞችን ለህግ አሳልፎ እንዲሰጥ ማድረግ ፣ ፀረሰላም ኃይሎች የሚንቀሳሰቁባቸውን ቀበሌያት ወሰን አካባቢ ህዝባዊ ሰራዊት እና ሚሊሻ ማደራጀት እንደሚገባ ገልጸዋል።
በሰላም ግንባታ ላይ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሚናቸውን እንዲጫወቱ ጠይቀዋል።
መከላከያ ለሚሰራው ኦፕሬሽን አዋሳኝ ቀበሌያት ያለው ህዝብ እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ ፥ " የተጀመረውን የአመራር ለአመራር እርስ በእርስ ግንኙነት ለማደናቀፍ የሚሰራ ፀረ ሰላም አለ " ብለዋል።
በመሆኑን የፀጥታ መዋቅሩ በተጠንቀቅ መቆም አለበት ሲሉ አስገንዝበዋል።
ሁለቱም መዋቅር አመራርና ፀጥታ አካላት እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሠራዊት በጋራ ተስማምተው በሚያስቀምጡት የሰዓት ገደብ መሰረት ከኬሌ - ዲላ መንገድ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ገልጸዋል።
" ከዛሬ ጀምሮ በቀጠናው የሰው ነፍስ የሚያጠፉ ንብረት የሚዘርፉ በኮሬ፣ ቡርኪና ጉጂ ስም የሚነግዱ ህገወጦች ወደ ቤት ግቡ " ሲሉ አሳስበዋል።
#KooreZone #BurjiZone #WestGujii #FDREDefenseForce
@tikvahethiopia
❤151🙏23😡23🕊18👏15🤔10🥰3😢3💔3😱1😭1
TIKVAH-ETHIOPIA
ነዋሪዎች እየተካሄደ ነው ስላሉት አፈሳ ምን አሉ ? በተለያዩ ከተሞች ወጣቶች በግዳጅ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እየተያዙ እየተወሰዱ መሆኑን ነዋሪዎች ቅሬታ አቅርበዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው በባህር ዳር፣ አዴትና ሞጣ እንዲሁም ጋይንት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎች " በ20ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ ያሉ ወጣቶችን የመከላከያና የአድማ ብተና መለዮ የለበሱ የመንግስት የፀጥታ አካላት ወጣቶችን እያፈሱ እስር…
የመከላከያ እና የኢሰመኮ ምላሽ ምንድነው ?
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮረኔል ጌትነት አዳነ ከቀናት በፊት በወቅታዊ የጸጥታ ጉዳይ ላይ ለመከላከያ ቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ ላይ የሰራዊት ምልመላን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
" የመከላከያ ሰራዊት ህገ-መንግስታዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በተፈጥሮም ሆነ በሰው ሰራሽ ነገር የሚወጣን ሰው ለመተካት እንዲሁም ሚዛን የጠበቀ የኃይል አሰላለፍ ታሳቢ ያደረገ የሰራዊት ዝግጅት ያስፈልጋል " ሲሉ የምልመላ አስፈላጊነትን ጠቅሰዋል።
ኮ/ል ጌትነት፥ " ተቋሙ በሚያወጣው መደበኛ የምልመላ መስፈርት ወጣቶችን ወደ ሰራዊቱ መቀላቀል በየትም ዓለም አቀፋዊ አሰራር ያለ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ዳይሬክተሩ የምልመላ መስፈርቶች ብለው ካቀረቧቸው በዋናነት ፦
- ህገ-መንግስቱን የተቀበሉ፤
- ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆነ፤
- ሀገራቸውን ለማገልገል ሙሉ ፈቃደኛ የሆኑ፤
- ከማንኛውም ፖለቲካ ድርጅቶች ወገኝተኝነት ነጻ የሆኑ፤
- ስልጠናውን ከወሰዱ በኋላ 7 ዓመት ለማገልገል ውል የሚገቡ፤
- ከወንጀል ነጻ የሆኑ፤
- የሚወጡትን አካላዊ መስፈርቶች የሚያሟሉ የሚሉት በጥቂቱ የሚጠቀሱት ናቸው።
የምልመላ አሰራሩን በተመለከተ ዳይሬክተሩ ምን አሉ ?
የምልመላ ሂደቱ በወረዳ እና በቀበሌ ያሉ የፀጥታ እና የመስተዳድር አካላት በኮሚቴ ሆነው የሚያከናውኑት ነው ሲሉ አፈጻጸሙን በተመለከተም ለመከላከያ ሪፖርት የሚቀርብበት መሆኑን አንስተዋል።
ምልመላው የብሔር ሚዛናዊ ተዋጽኦ ያካተተ መሆን ስላለበትም ከብሔራዊ ስታስቲክስ ቢሮ በተወሰደ ቁጥራዊ የክልሎች መረጃ መሰረት መከላከያ ለክልሎች ኮታ እንደሚሰጥ ነው የተናገሩት።
አፈጻጸምን በተመለከተ ኮ/ል ጌትነት " እንደ አቅሙ ነው " በሚል የገለጹ ሲሆን ከወረዳ እና ቀበሌ የተደረገው ምዝገባ እንዲሁ የሚወሰድ ሳይሆን በዞን ደረጃ እንዲሁም ማሰልጠኛ ሲደርሱ የማጣራት ሥራ እንደሚሰራም አንስተዋል።
በዚህም የክልሎች ተወካዮች ባሉበት ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ተሰይሞ በፈቃዱ መምጣቱን ብቻ ሳይሆን ከተቀነሰም የተቀነስኩበት አግባብ ትክክል አይደለም ብሎ ቅሬታ ማቅረብ እንደሚቻል ነው ያነሱት።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በጉዳዩ ላይ ምን አለ ?
በየአካባቢው የሚስተዋሉ የወጣቶች አፈሳ ስለመኖሩ ቅሬታ ደርሷቸው እንደሆነ ከሪፖርተር ጋዜጣ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።
" ክትትሉ አልቆ የወጣ የተጠናቀቀ ዶክመንት የለንም። ሚዲያ ላይ የምንሰማው ነገር ስላለ ይሄን ይዘ [ከቀናት በፊት] ከሀገር ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሞያዎች ጋር ተወያይተናል።
በእነሱ በኩል የምልመላ መስፈርቱ ላይ፤ የምልመላ አካሄዱ ላይ ምንም ችግር የለም ችግር ያለው ምንአልባት ታች አከባቢ የአስተዳደር አካላት ምልመላውን ሲያካሄዱ የሚፈጸሙ ትክክል ያልሆኑ አካሄዶች ካሉ በጋራ ለመስራት ተስማምተን ነው የተለያየነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ኢሰመኮ ይህ ድርጊት ስለመፈጸሙ መረጃው ኖሮት ነው ውይይቱን ያደረገው ?
ዋና ኮሚሽነሩ በዚህ ጉዳይ ላይ በሰጡት ቃል ኮሚሽኑ ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን በመከተል አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እየተካሄደ መሆን አለመሆኑን እያጣራ እንደሚገኝ እና ሥራው ሲጠናቀቅ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
በዚህም ኮሚሽኑ ዓለም አቀፍ ስታንደርዱን ጠብቆ የቀረበ ዶክመንት ወይም Standard of Proof ጨርሶ መደምደሚያ ላይ አለመድረሱን ጠቁመው ይህ ሲጠናቀቅ በየአራት ወሩ በሚወጣው ሪፖርት አካተው እንደሚያወጡ ተናግረዋል።
ውይይቱን በተመለከተ ግን ኮሚሽነሩ " ሚዲያ ላይ የምንሰማው ነገር ስላለ እሱን ይዘን ነው ከመከላከያ ሚኒስቴር ባለሞያዎች ጋር የተወያየነው " ሲሉ ውይይቱ በግል ተነሳሽነት ጭምር የተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
#FDREDefenseForce #EHRC
@tikvahethiopia
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮረኔል ጌትነት አዳነ ከቀናት በፊት በወቅታዊ የጸጥታ ጉዳይ ላይ ለመከላከያ ቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ ላይ የሰራዊት ምልመላን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
" የመከላከያ ሰራዊት ህገ-መንግስታዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በተፈጥሮም ሆነ በሰው ሰራሽ ነገር የሚወጣን ሰው ለመተካት እንዲሁም ሚዛን የጠበቀ የኃይል አሰላለፍ ታሳቢ ያደረገ የሰራዊት ዝግጅት ያስፈልጋል " ሲሉ የምልመላ አስፈላጊነትን ጠቅሰዋል።
ኮ/ል ጌትነት፥ " ተቋሙ በሚያወጣው መደበኛ የምልመላ መስፈርት ወጣቶችን ወደ ሰራዊቱ መቀላቀል በየትም ዓለም አቀፋዊ አሰራር ያለ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ዳይሬክተሩ የምልመላ መስፈርቶች ብለው ካቀረቧቸው በዋናነት ፦
- ህገ-መንግስቱን የተቀበሉ፤
- ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆነ፤
- ሀገራቸውን ለማገልገል ሙሉ ፈቃደኛ የሆኑ፤
- ከማንኛውም ፖለቲካ ድርጅቶች ወገኝተኝነት ነጻ የሆኑ፤
- ስልጠናውን ከወሰዱ በኋላ 7 ዓመት ለማገልገል ውል የሚገቡ፤
- ከወንጀል ነጻ የሆኑ፤
- የሚወጡትን አካላዊ መስፈርቶች የሚያሟሉ የሚሉት በጥቂቱ የሚጠቀሱት ናቸው።
የምልመላ አሰራሩን በተመለከተ ዳይሬክተሩ ምን አሉ ?
የምልመላ ሂደቱ በወረዳ እና በቀበሌ ያሉ የፀጥታ እና የመስተዳድር አካላት በኮሚቴ ሆነው የሚያከናውኑት ነው ሲሉ አፈጻጸሙን በተመለከተም ለመከላከያ ሪፖርት የሚቀርብበት መሆኑን አንስተዋል።
ምልመላው የብሔር ሚዛናዊ ተዋጽኦ ያካተተ መሆን ስላለበትም ከብሔራዊ ስታስቲክስ ቢሮ በተወሰደ ቁጥራዊ የክልሎች መረጃ መሰረት መከላከያ ለክልሎች ኮታ እንደሚሰጥ ነው የተናገሩት።
አፈጻጸምን በተመለከተ ኮ/ል ጌትነት " እንደ አቅሙ ነው " በሚል የገለጹ ሲሆን ከወረዳ እና ቀበሌ የተደረገው ምዝገባ እንዲሁ የሚወሰድ ሳይሆን በዞን ደረጃ እንዲሁም ማሰልጠኛ ሲደርሱ የማጣራት ሥራ እንደሚሰራም አንስተዋል።
በዚህም የክልሎች ተወካዮች ባሉበት ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ተሰይሞ በፈቃዱ መምጣቱን ብቻ ሳይሆን ከተቀነሰም የተቀነስኩበት አግባብ ትክክል አይደለም ብሎ ቅሬታ ማቅረብ እንደሚቻል ነው ያነሱት።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በጉዳዩ ላይ ምን አለ ?
በየአካባቢው የሚስተዋሉ የወጣቶች አፈሳ ስለመኖሩ ቅሬታ ደርሷቸው እንደሆነ ከሪፖርተር ጋዜጣ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።
" ክትትሉ አልቆ የወጣ የተጠናቀቀ ዶክመንት የለንም። ሚዲያ ላይ የምንሰማው ነገር ስላለ ይሄን ይዘ [ከቀናት በፊት] ከሀገር ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሞያዎች ጋር ተወያይተናል።
በእነሱ በኩል የምልመላ መስፈርቱ ላይ፤ የምልመላ አካሄዱ ላይ ምንም ችግር የለም ችግር ያለው ምንአልባት ታች አከባቢ የአስተዳደር አካላት ምልመላውን ሲያካሄዱ የሚፈጸሙ ትክክል ያልሆኑ አካሄዶች ካሉ በጋራ ለመስራት ተስማምተን ነው የተለያየነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ኢሰመኮ ይህ ድርጊት ስለመፈጸሙ መረጃው ኖሮት ነው ውይይቱን ያደረገው ?
ዋና ኮሚሽነሩ በዚህ ጉዳይ ላይ በሰጡት ቃል ኮሚሽኑ ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን በመከተል አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እየተካሄደ መሆን አለመሆኑን እያጣራ እንደሚገኝ እና ሥራው ሲጠናቀቅ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
በዚህም ኮሚሽኑ ዓለም አቀፍ ስታንደርዱን ጠብቆ የቀረበ ዶክመንት ወይም Standard of Proof ጨርሶ መደምደሚያ ላይ አለመድረሱን ጠቁመው ይህ ሲጠናቀቅ በየአራት ወሩ በሚወጣው ሪፖርት አካተው እንደሚያወጡ ተናግረዋል።
ውይይቱን በተመለከተ ግን ኮሚሽነሩ " ሚዲያ ላይ የምንሰማው ነገር ስላለ እሱን ይዘን ነው ከመከላከያ ሚኒስቴር ባለሞያዎች ጋር የተወያየነው " ሲሉ ውይይቱ በግል ተነሳሽነት ጭምር የተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
#FDREDefenseForce #EHRC
@tikvahethiopia
😡578❤81😭70🙏21💔17👏9🕊9🤔8🥰4😢4😱1