TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Passport
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለአዲስ አበባ አስቸኳይ ፓስፖርት አመልካቾች ባሰራጨው መልዕክት የአስቸኳይ ፖስፖርት ኦንላይን ሲስተም የተወሰነ ማሻሻያ ተደርጎበት ስራ መጀመሩን ገልጿል።
ከግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ሁሉም አመልካች በኦንላይን በማመልከት በቀጠሮ ቀኑ ብቻ ወደ ተቋሙ መሄድ መስተናገድ እንደሚችል አሳውቋል።
በኦን ላይን መሙላት ያልቻሉ አስቸኳይ ጉዳይ ያላቸው አመልካቾች በአካል መጥተው መስተናገድ እንደሚችሉ ገልጿል።
በተጨማሪ አገልግሎቱ ፥ " ከግንቦት 6/ 2017 ዓ/ም ጀምሮ መደበኛ የፓስፖርት አገልግሎት ከጠዋቱ 12:00 - 8:00 ሰአት ድረስ የአስቸኳይ ፓስፖርት አገልግሎት ደግሞ ከ9:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 4:00 ሰአት በሁለት ፈረቃ እንሰጣለን በቀጠሮ ቀናችሁ በፕሮግራሙ መሰረት ወደተቋማችን በመምጣት ተስተናገዱ " ብሏል።
" ከቀጠሮ ቀን ውጭ በተቋሙ አካባቢ መቆምም ሆነ አላስፈላጊ እንቅስቃሴ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ነው " ሲልም አሳስቧል።
#ICS
@tikvahethiopia
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለአዲስ አበባ አስቸኳይ ፓስፖርት አመልካቾች ባሰራጨው መልዕክት የአስቸኳይ ፖስፖርት ኦንላይን ሲስተም የተወሰነ ማሻሻያ ተደርጎበት ስራ መጀመሩን ገልጿል።
ከግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ሁሉም አመልካች በኦንላይን በማመልከት በቀጠሮ ቀኑ ብቻ ወደ ተቋሙ መሄድ መስተናገድ እንደሚችል አሳውቋል።
በኦን ላይን መሙላት ያልቻሉ አስቸኳይ ጉዳይ ያላቸው አመልካቾች በአካል መጥተው መስተናገድ እንደሚችሉ ገልጿል።
በተጨማሪ አገልግሎቱ ፥ " ከግንቦት 6/ 2017 ዓ/ም ጀምሮ መደበኛ የፓስፖርት አገልግሎት ከጠዋቱ 12:00 - 8:00 ሰአት ድረስ የአስቸኳይ ፓስፖርት አገልግሎት ደግሞ ከ9:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 4:00 ሰአት በሁለት ፈረቃ እንሰጣለን በቀጠሮ ቀናችሁ በፕሮግራሙ መሰረት ወደተቋማችን በመምጣት ተስተናገዱ " ብሏል።
" ከቀጠሮ ቀን ውጭ በተቋሙ አካባቢ መቆምም ሆነ አላስፈላጊ እንቅስቃሴ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ነው " ሲልም አሳስቧል።
#ICS
@tikvahethiopia
👏367❤100😡61🙏31😢21🕊13😭12🤔10🥰2😱2