TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
🚨#ትኩረት

ያቄር ገበሬ ማህበር ነዋሪዎች !

ያቄር በትግራይ ማእከላዊ ዞን ቆላ ተምቤን ወረዳ የምትገኝ የገጠር ቀበሌ ነች።

ቀበሌዋ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስምዋ ከደርቅ ተያይዞ ይነሳል።

የወረዳው አስተዳደር ፤ በቀበሌዋ የተከሰተው ድርቅ መፍትሄ ካልተበጀለት አስከፊ እልቂት ያስከትላል በማለት መግለጫ አውጥቷል።

" በቀበሌዋ እስከ ሀምሌ 23/2017 ዓ.ም ዝናብ ስላልዘነበ ገበሬዎቹ የነበራቸው የምግብ እህልና የእንስሳት ቀለብ ተሟጦ አልቋል። በዚሁ ምክንያት ፦
➡️ 184 ከብቶች
➡️ 900 አህዮች
➡️ ከ17 ሺህ በላይ በጎችና ፍየሎች አልቀዋል። 200 ያህል የንብ ቆፎ ጠፍቷል " ሲል ገልጿል።

" በቀበሌው ነዋሪዎች በተለይ ደግሞ በአረጋውያንና ህፃናት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የሚያመልክቱ የሰውነት መጠውለግና የማበጥ ምልክቶች መታየት ጀምረዋል " ሲልም አክሏል።

በዝናብ እጦት የተከሰተው ድርቅ በ700 ሄክታር የተዘራ እህል ከጥቅም ውጭ ማድረጉ የሚጠቅሰው ወረዳው ሽሉም እምኒ፣ ምውፃእ ወርቂ ፣ ዘላቅመ ፣ ዓረና ፣ ነዊ ፣ ጯሞ ፣ ደደረ ፣ ስምረት ጉያ በሚባሉ የቀቤዋ ጎረቤት መንደሮችም ተመሳሳይ ምልክቶች መኖራቸው አስታውቋል።

በቀበሌዋ የተከሰተው ድርቅ በሰውና እንስሳት ላይ አሁን ካለው የባሰ አስከፊ አደጋ ከማድረሱ በፊት እንዲገታ ለተለያዩ ለጋሾች ጥያቄ ማቅረቡ የጠቅሰው ወረዳ እስከ አሁን የተሰጠ አስቸኳይ ምላሽ ባለመኖሩ ምክንያት ሁኔታው እጅግ አሳሳቢ እንዳደረገው አመልክቷል።

በያቄር ቀበሌ ገበሬ ማህበር ተከስተዋል ስለተባለው አደገኛ ድርቅ አሰመልክቶ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበለት የክልሉ የአደጋና ስጋት መከላከል ኮሚሽን ጉዳዩ እየተከታተለው እንደሆነ ጠቅሷል።

ያለውን ሁኔታ በአካል ተመልክቶ በጥልቀት የሚያጠና ቡድን መላኩንና ከሰኞ ሀምሌ 28/2017 ዓ.ም ጀምሮ የተሟላ መረጃ እንደሚሰጥ ቃል ገብቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
1😭1.09K570💔85😢72🕊44🙏35😡15🥰14👏12🤔1