አሜሪካ በኤርትራ ጨምሮ በሌሎችም ሀገራት ያሉ ኤምባሲዎቿን ልትዘጋ ነው።
አሜሪካ ወደ 30 የሚጠጉ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ዲፕሎማቲክ ጽሕፈት ቤቶቿን ልትዘጋ መሆኑን ሮይተርስ የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ሰነድን ጠቅሶ ዘገበ።
የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር አብዛኞቹ በአፍሪካ እና በአውሮፓ የሚገኙ ቢያንስ 27 የአሜሪካ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎችን የሚዘጋ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ጎረቤት ሀገር #ኤርትራ አንዷ ናት።
በውሳኔው መሠረት ይዘጋሉ የተባሉት አስሩ የአሜሪካ ኤምባሲዎች ፦
- በኤርትራ፣
- በግሪናዳ፣
- በሌሶቶ፣
- በማዕካላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣
- በሉክዘንበርግ፣
- በሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ፣
- በጋምቢያ፣
- በደቡብ ሱዳን፣
- በማልታ እና በማልዲቭስ የሚገኙ መሆናቸውን ሮይተርስ የተመለከተው ሰነድ ያመለክታል።
ከሚዘጉት ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎች ባሻገር ኤምባሲ እና በርካታ ቆንስላዎችን በመያዝ ግዙፍ የዲፕሎማቲክ ሥራ በሚከናወንባቸው እንዳ ጃፓን እና ካናዳ ያሉትን ተልዕኮዎች በማዋሃድ መጠናቸውን የመቀነስም ሐሳብ አለ።
ሰነዱ ከፍተኛ ወጪ በማስወጣት ውድ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ የተመደበባቸው ናቸው ያላቸውን በሞቃዲሾ ሶማሊያ እና በኢራቅ ያሉ የዲፕሎማቲክ አባላትን መጠን የመቀነስ ሐሳብም መቅረቡን አመልክቷል።
ዶናልድ ትራምፕ ወደ ፕሬዝዳንትነት ከተመለሱ በኋላ የአሜሪካ መንግሥት በተለያዩ መስኮች ከአገሪቱ ፍላጎት ጋር አይጣጣሙም ያላቸውን ተቋማት በመዝጋት እና እርዳታዎችን በማቋረጥ ላይ ይገኛል።
የትራምፕ የቅርብ ሰው በመሆኑት ማርኮ ሩቢዮ የሚመራው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በጀት እስከ ግማሽ የሚደርሰውን እንደሚቀነስ ሮይተርስ የተመለከተውን የመሥሪያ ቤቱን ሰነድ ጠቅሶ አመልክቷል።
በዚህም ሳቢያ በበርካታ አገራት የሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎችን የመዝጋት ሐሳብ ሀሳብ ነው ያለው።
የአሜሪካ መንግሥት ለውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ከሚያወጣው ገንዘብ ወደ 30 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ለመቀነስ አቅዶ የበጀት ጥያቄውን ለአገሪቱ ምክር ቤት ለማቅረብ እየተዘጋጀ ነው።
መረጃው የሮይተርስ እና ቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
አሜሪካ ወደ 30 የሚጠጉ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ዲፕሎማቲክ ጽሕፈት ቤቶቿን ልትዘጋ መሆኑን ሮይተርስ የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ሰነድን ጠቅሶ ዘገበ።
የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር አብዛኞቹ በአፍሪካ እና በአውሮፓ የሚገኙ ቢያንስ 27 የአሜሪካ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎችን የሚዘጋ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ጎረቤት ሀገር #ኤርትራ አንዷ ናት።
በውሳኔው መሠረት ይዘጋሉ የተባሉት አስሩ የአሜሪካ ኤምባሲዎች ፦
- በኤርትራ፣
- በግሪናዳ፣
- በሌሶቶ፣
- በማዕካላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣
- በሉክዘንበርግ፣
- በሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ፣
- በጋምቢያ፣
- በደቡብ ሱዳን፣
- በማልታ እና በማልዲቭስ የሚገኙ መሆናቸውን ሮይተርስ የተመለከተው ሰነድ ያመለክታል።
ከሚዘጉት ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎች ባሻገር ኤምባሲ እና በርካታ ቆንስላዎችን በመያዝ ግዙፍ የዲፕሎማቲክ ሥራ በሚከናወንባቸው እንዳ ጃፓን እና ካናዳ ያሉትን ተልዕኮዎች በማዋሃድ መጠናቸውን የመቀነስም ሐሳብ አለ።
ሰነዱ ከፍተኛ ወጪ በማስወጣት ውድ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ የተመደበባቸው ናቸው ያላቸውን በሞቃዲሾ ሶማሊያ እና በኢራቅ ያሉ የዲፕሎማቲክ አባላትን መጠን የመቀነስ ሐሳብም መቅረቡን አመልክቷል።
ዶናልድ ትራምፕ ወደ ፕሬዝዳንትነት ከተመለሱ በኋላ የአሜሪካ መንግሥት በተለያዩ መስኮች ከአገሪቱ ፍላጎት ጋር አይጣጣሙም ያላቸውን ተቋማት በመዝጋት እና እርዳታዎችን በማቋረጥ ላይ ይገኛል።
የትራምፕ የቅርብ ሰው በመሆኑት ማርኮ ሩቢዮ የሚመራው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በጀት እስከ ግማሽ የሚደርሰውን እንደሚቀነስ ሮይተርስ የተመለከተውን የመሥሪያ ቤቱን ሰነድ ጠቅሶ አመልክቷል።
በዚህም ሳቢያ በበርካታ አገራት የሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎችን የመዝጋት ሐሳብ ሀሳብ ነው ያለው።
የአሜሪካ መንግሥት ለውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ከሚያወጣው ገንዘብ ወደ 30 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ለመቀነስ አቅዶ የበጀት ጥያቄውን ለአገሪቱ ምክር ቤት ለማቅረብ እየተዘጋጀ ነው።
መረጃው የሮይተርስ እና ቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
👏340❤128🤔57😢32😱23🕊21🙏16😭8😡8🥰7
" ስምምነቱን ተከትሎ ተሽከርካሪዎቹ ተለቀዋል " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ፅ/ቤት
ወደ ትግራይ ክልል ሲጓዙ አፋር ላይ ለቀናት ክልከላ የተደረገባቸው ተሽከርካሪዎች እንዲለቀቁ ተወሰነ።
ውሳኔውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ጋር መወያየታቸውን ተከትሎ ነው ተግባራዊ የሆነው።
ፕሬዚዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ግንቦት 23/ 2017 ዓ/ም ከኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ጋር ውይይት አድርገዋል።
በዚህም ከግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በአፋር በኩል ወደ ትግራይ ሲጓዙ ክልከላ የተደረገባቸው የጭነት ተሽከርካሪዎች የተከለከሉበት ምክንያት የጫኑት የንግድ እቃ ከትግራይ አልፎ በኮንትሮባንድ መልክ ወደ #ኤርትራ ሊሻገር ይችላል ከሚል ጥርጣሬ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ተገልጿል።
ሁለቱም ኃላፊዎች በውይይታቸው የመረጃው እውነትነቱ ምን ድረስ እንደሆነ የሚያጣራ ከፌደራል ፖሊስ እና ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተውጣጣ ኮሚቴ ጉዳዩን እንዲመረምረው ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የኮሚቴው የምርመራ ውጤት መሰረት በማድረግ የቁጥጥር ስርአት እንዲዘረጋ እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ይህን የማከናወን ተግባርና ኃላፊነት ደግሞ በዋናነት የጋራ ኮሚቴው እንዲሆን ተወስኗል።
ስምምነቱን ተከትሎ ተሽከርካሪዎቹ ተለቀዋል።
በቀጣይም ተመሳሳይ ችግር እንዳያጋጥም ኃላፊዎቹ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤታ ያሰራጨው መረጃ አመልክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ወደ ትግራይ ክልል ሲጓዙ አፋር ላይ ለቀናት ክልከላ የተደረገባቸው ተሽከርካሪዎች እንዲለቀቁ ተወሰነ።
ውሳኔውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ጋር መወያየታቸውን ተከትሎ ነው ተግባራዊ የሆነው።
ፕሬዚዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ግንቦት 23/ 2017 ዓ/ም ከኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ጋር ውይይት አድርገዋል።
በዚህም ከግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በአፋር በኩል ወደ ትግራይ ሲጓዙ ክልከላ የተደረገባቸው የጭነት ተሽከርካሪዎች የተከለከሉበት ምክንያት የጫኑት የንግድ እቃ ከትግራይ አልፎ በኮንትሮባንድ መልክ ወደ #ኤርትራ ሊሻገር ይችላል ከሚል ጥርጣሬ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ተገልጿል።
ሁለቱም ኃላፊዎች በውይይታቸው የመረጃው እውነትነቱ ምን ድረስ እንደሆነ የሚያጣራ ከፌደራል ፖሊስ እና ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተውጣጣ ኮሚቴ ጉዳዩን እንዲመረምረው ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የኮሚቴው የምርመራ ውጤት መሰረት በማድረግ የቁጥጥር ስርአት እንዲዘረጋ እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ይህን የማከናወን ተግባርና ኃላፊነት ደግሞ በዋናነት የጋራ ኮሚቴው እንዲሆን ተወስኗል።
ስምምነቱን ተከትሎ ተሽከርካሪዎቹ ተለቀዋል።
በቀጣይም ተመሳሳይ ችግር እንዳያጋጥም ኃላፊዎቹ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤታ ያሰራጨው መረጃ አመልክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤1.18K🕊90😡77🙏50😢31🤔23🥰13💔8👏6