TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ነዳጅ #ቤንዚን

በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተባባሰ የመጣዉን የነዳጅ ምርቶች ሕገወጥ ግብይት ለመከላከልና በየከተማዉ የሚስተዋሉ ረጃጅም ሰልፎችን በማስቀረትና የተጠቃሚዎችን ቅሬታ ለመፍታት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታወቀ።

የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሳህረላ አቡዱላሂ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ በነዳጅ ምርቶች በተለይ በቤንዚን አቅርቦትና ስርጭት በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች ቅሬታዎች እንደሚነሱና ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ስለመኖራቸው ገልፀዋል።

" አንዱና መሠረታዊዉ ምክንያት ከዚህ ቀደም 80 በመቶ የሚሆነዉ የሀገራችንን የነዳጅ ፍጆታ ይሸፍን የነበረዉ በሱዳን ወደብ የሚገባዉ ቢሆንም አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ጅቡቲ ዞሯል " ብለዋል።

" ወደቡ ላይ ከፍተኛ መጨናነቆች ይስተዋላሉ የጅቡቲዉ ወደብ ከ20 ዓመታት በፊት የነበረን የሀገራችንን የነዳጅ ፍላጎትና አቅርቦትን ለማስተናገድ ታስቦ የተሰራ ስለነበር በቴርሚናሉ ላይ ያለዉ መጨናነቅ መንግስት በከፍተኛ ድጎማ የሚያስገባቸዉ የነዳጅ ምርቶች በተለይም በቤንዚን አቅርቦትና ስርጭት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አሳድሯል " ሰሉ ገልፀዋል።

መንግስት አሁንም ድረስ ከፍተኛ የገንዘብ ድጎማ በማድረግ ወደ ሀገር ዉስጥ በሚያስገባቸዉ የነዳጅ ምርቶች ላይ አንዳንድ አከባቢዎች ሰዉ ሰራሽ አቅርቦት እጥረት እንዲፈጠር በማድረግ የግል ጥቅማቸዉን ለማካበት የሚጥሩ አካላት መኖራቸዉን ማረጋገጣቸውን ወ/ሮ ሰሃረላ ተናግረዋል።

በቴክኖሎጂ የታገዘ ቁጥጥርና የአሠራር ስርዓት በመዘርጋት ሕገወጥ ግብይቱን የመከላከልና በህገወጦች ላይ እርምጃ የመዉሰዱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

" ከአቅርቦቱ ባሻገር ወደ ሀገር ዉስጥ የገባዉን
ቤንዚን በአግባቡ በማሰራጨቱ በኩል በየክልሉ የተለያዩ ክፍተቶች አሉ " ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሁሉም ማዕቀፎች ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል መወሰድ በመጀመሩ በርከት ያሉ የንግድና ገበያ ልማት ባለሙያዎች ማደያዎችን ጨምሮ በሕገወጥ ግብይቱ ሰንሰለቱ ተሳታፊ የሆኑ አካላት ላይ በየደረጃው እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አብራርተዋል።

ለአብነትም በሲዳማ ክልል ብቻ የግብይት ስርዓቱ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ በመፍጠር ሰዉ ሰራሽ እጥረት እንዲስፋፋ ያደረጉ 9 ማደያዎች ላይ ነዳጅ እንዳያገኙ እገዳ እንደተላለፈባቸው ገልፀዋል።

በሌሎችም ክልልሎች በዚህ ረገድ እየተከናወኑ ያሉ የቁጥጥርና ክትትል ተግባራት በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀዉ አዲሱ የነዳጅ ምርቶች ቁጥጥር አዋጅ ጋር ተዳምረዉ በዘርፉ የሚስተዋለዉን ችግር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንሰዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
😁305😡8167😭16🤔14🙏9🕊8👏6🥰2😢2
#አፋር #ቤንዚን

“አንድ ሊትር ቤንዚን በብላክ ማርኬት ከ250 ብር በላይ ገዝተን ሰርትን መተዳደር በጣም ከብዶናል” - የሰመራ ከተማ አሽከርካሪዎች

“ባለፉት ስድስትና ሰባት ቀናት ውስጥ በጣም ከፍተኛ የነዳጅ እጥረት አለ” - የአፋር ክልል ንግድ ቢሮ

በአፋር ክልል በተለይም ሰመራ ከተማ ያሉ ባለሦስት እግር ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች ቤንዚን ከማደያ እንዳይቀዱ በመከልከላቸው አንድ ሊትር ቤንዚን በችርቻሮ ከ250 ብር ገዝተው ሰርተው የኑሮ ውድነቱን መቋቋም ባለመቻላቸው ተማረሩ።

የከተማዋ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ?

“እዚህ ከተማ እየተደረገ ያለው፥ የነዳጅ ቦቴዎች አልፎ አልፎ ይመጣሉ፡፡ ያም ማደያ ጉድጓድ ውስጥ ይገለበጥና እንደገና ወደ ጀሪካን እየቀዱ በማደያ ቤቱ አጠገብ ባሉ የችርቻሮ ኮንቴነሮች ይሸጣል።

እዛ ላይ በ200 ብር ነው አንድ ሊትር
ቤንዚን የምንቀዳው፡፡ ወደ ደረቅ ወደብ ማደያዎች ያሉም እንደዚሁ በብላክ ማርኬት ነው የሚገዙት፡ 

በችርቻሮ የሚሸጡልን ከማደያው በገሃድ በጀሪካን ቀድተው ነው የሚረከቡት፡፡ የሚቸረችሩት አንድ ሊትር
ቤንዚን ከ260 ብር በላይ ነው የሚሸጡት።

ከማደያ ላይ መቅዳት አይታሰብም፤ አንድም ቀን ቀድተን አናውቅም፡፡ 

መፍትሄ ተሰጥቶት የምንሰራበት ሁኔታ ይመቻችልን፡፡ በዚህ ኑሮ ውድነት
ቤንዚን በብላክ ማርኬት ከ250 ብር በላይ ገዝተን ሰርትን ገቢ ማግኘትና መተዳደር በጣም ከብዶናል፡፡ ከምንለው በላይ ነው ሁሉም የተቸገረው” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የባለሦስት እግር ሹፌሮች፣ “ ቤንዚን ማደያ እንዳንቀዳ ተከልክለናል ፤ በችርቻሮና ኮንትሮባንድ ዋጋ ነው የምንቀዳው ” ብለዋል፤ ጉዳዩን ተመልክታችሁት ነበር? ሲል የአፋር ክልል ንግድ ቢሮን ምላሽ ጠይቋል።

የክልሉ የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አሕመድ አብዱልቃድር ምን መለሱ ?

“ ማደያ ላይ ቤንዚን ድሮም አይቀዳም፡፡ ምክንያቱም በጣም ኃይለኛ ሙቀት ስላለ ጉድጓድ ላይ ቤንዚን ከተቀዳ አደጋ ያደሰርሳል።

ነገር ግን ማደያዎች አውርደው እዛው አካባቢ ነው ሹሬሮች የሚቀዱት፡፡ በጣም ኃይለኛ ሙቀት ስላለ ከዚያ አንጻር የሚቀዳው እንደዛ ነው፡፡ አዋሽ ግን በማደያ ነው የሚቀዳው ቀዝቀዝ ስለሚል፡፡

ሰመራ ከተማ ኮንትባንድ የለም፡፡ ግን የነዳጅ እጥረት አለ በኃይለኛ፡፡ በተለይ ሰማራ የክልሉ ዋና ከተማ ብቻ ሳይሆን የውጭ ንግድ የሚያልፈበት ከተማ እንደመሆኑ መጠን ባለፉት ስድስትና ሰባት ቀናት ውስጥ በጣም ከፍተኛ የነዳጅ እጥረት አለ።

ትልልቅ ካምፓኒዎች ጋር ለማዳረስ ጥረት እየተደረገ ነው ያለው፤ ኖክና ኦይልቪያ፡፡ ግን ሁሉም ማደያዎች ካላመጡ ወዲያው ነው የሚያልቀው፡፡ አብዛኛዎቹ መኪኖች ከአዋሽ እዚህ ለመቅዳት ነው የሚመጡት፡፡

ለመቅዳት ሲመጡም አንድ መኪና በቀን ማግኘት ያለባቸው ሰዎች የሚያገኙት በ2 ቀናት፣ በ3 ቀናት አንድ መኪና ከሆነ ሎዱ ይበዛል። እጥረቱን ከነዳጅና ኢነርጅ ባለስልጣን ጋር ሆነን ለመፍታት ጥረት እያደረግን ነው ”
ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭491172😁84🙏41😱39😢26🤔20👏19🕊19😡12🥰6