#ጥናት🤖
" የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) መሳሪያዎች የሰዎችን የማመዛዘን ብቃት እየቀነሱት ነዉ " - ጥናት
በቅርቡ የካርኔጊ ሜሎን ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ማይክሮሶፍት በጋራ የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) በሰዎች የማገናዘብ አቅም ላይ ስለሚኖረዉ ተፅዕኖ አንድ ጥናት አድርገዉ ነበር።
ይህ ጥናት ከፈረንጆቹ 2024 እስከ 2025 የተካሄደ ሲሆን ባለፈው ሚያዚያ ወር በጃፓን ዮኮሀማ በተካሄደ ኮንፍረንስ ላይ በይፋ ለህዝብ የቀረበ ነው።
319 ሰዎችን ያካተተዉ ይህ ጥናት ስራቸዉ ጥልቅ የሆነ ማሰብን ይጠይቃል የተባሉ ሰዎችን አካቷል።
የጥናቱ የተገኙ ግኝቶች ምንድን ናቸው ?
በዚህ ጥናት በዋናነት ሶስት ግኝቶች ተቀምጠዋል።
1ኛ. ጥናቱ ከተደረገባቸው ሰዎች አብዛኞቹ ነገሮች ላይ በጥልቀት ማሰብ እና ትኩረት ማድረግ ላይ እንደሚቸገሩ የጥናቱ ውጤት ያሳያል።
" የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) መሳሪያዉ ይመልሰዋል " ብለዉ ስለሚያስቡ ነገሮችን በጥልቀት የመመርመር ፍላጎት መቀነስም ታይቶባቸዋል።
2ኛ. ከመጠን ያለፈ እምነት በሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) መሳሪያዎች ላይ መጣል ሲሆን ጥናቱ የተደረገባቸው ሰዎች ከመሳሪያዉ የሚገኙ ዉጤቶች ላይ ከፍተኛ የሆነ መተማመን እንዳላቸዉ ያሳያል።
ውጤቶቹንም እውነተኛነታቸዉን ለማረጋገጥ ሌላ ተጨማሪ ምንጮችን በማየት ለማረጋገጥ እንደማይሞክሩ ውጤቱ ያመለክታል።
3ኛ. የጥናቱ ውጤት ሰዎች ጥልቅ እና የተወሳሰቡ የሚመስሉ ነገሮችን ከማሰብ እና ምክንያታዊ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ከሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) መሳሪያዎች የሚወጡ ቀላል እና መሰረታዊ ስህተቶችን በማረም ላይ ያተኩራሉ ብሏል።
እንዲሁም የራሳቸዉን አስተሳሰብ በጥቂቱ ስለሚያቀርቡ የግለሰቡን ሀሳብ የማመንጨት ተፈጥሯዊ ብቃቱን እንደሚያሳጣዉ ጥናቱ ይገልጻል።
በጥናቱ መሰረት ከመረጃ ጋር የተያያዙ ስራዎች ከሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) መሳሪያዎች ጥቅም ላይ መዋል በኋላ መረጃን ከመሰብሰብ ወደ ማረጋገጥ መዞራቸውን ያነሳል።
ችግር ፈቺ በሆኑ የሥራ ቦታዎችም ቀጥታ ችግሩን ከመፍታት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምክሮቸን ወደመቀበል ዞረዋል ተብሏል።
በጥናቱ ከተሳተፉ 319 ሰዎች ውስጥ 83 ያህሉ በሰው ሰራሽ አስተውሎት መሳሪያዎች ላይ ያላቸው መተማመን የማገናዘብ አቅማቸውን እንዳዳከመው አምነዋል።
ከዚህ በተጨማሪ 72 ሰዎች ከሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ያገኙት ምላሽ ስህተት እያለው እንኳን ለማረም እንደማይችሉ በጥናቱ ተመላክቷል።
በአጠቃላይ የጥናቱ ማጠቃለያ ሰዎች በስራ ቦታ ላይ ያላቸዉ የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) መሳሪያዎች አጠቃቀም የሰዎችን ምክንያታዊ የአስተሳሰብ አቅም እየቀነሰዉ መምጣቱን ያሳያል።
ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ተጠቃሚዎች ከሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት መሳሪያዎች በሚመነጩ መልሶች ላይ መተማመናቸው ነው።
በተጨማሪም ከመተንተን ይልቅ ከሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት የሚገኙ ውጤቶችን ወደ ማረጋገጥ ፣ ማቀናጀት እና መሰረታዊ ሰህተቶችን ወደ ማረም መዞራቸው መሆኑን ጥናቱ ያሳያል።
#TikvahEthiopiaFamliyAA
Via @TikvahethMagazine
" የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) መሳሪያዎች የሰዎችን የማመዛዘን ብቃት እየቀነሱት ነዉ " - ጥናት
በቅርቡ የካርኔጊ ሜሎን ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ማይክሮሶፍት በጋራ የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) በሰዎች የማገናዘብ አቅም ላይ ስለሚኖረዉ ተፅዕኖ አንድ ጥናት አድርገዉ ነበር።
ይህ ጥናት ከፈረንጆቹ 2024 እስከ 2025 የተካሄደ ሲሆን ባለፈው ሚያዚያ ወር በጃፓን ዮኮሀማ በተካሄደ ኮንፍረንስ ላይ በይፋ ለህዝብ የቀረበ ነው።
319 ሰዎችን ያካተተዉ ይህ ጥናት ስራቸዉ ጥልቅ የሆነ ማሰብን ይጠይቃል የተባሉ ሰዎችን አካቷል።
የጥናቱ የተገኙ ግኝቶች ምንድን ናቸው ?
በዚህ ጥናት በዋናነት ሶስት ግኝቶች ተቀምጠዋል።
1ኛ. ጥናቱ ከተደረገባቸው ሰዎች አብዛኞቹ ነገሮች ላይ በጥልቀት ማሰብ እና ትኩረት ማድረግ ላይ እንደሚቸገሩ የጥናቱ ውጤት ያሳያል።
" የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) መሳሪያዉ ይመልሰዋል " ብለዉ ስለሚያስቡ ነገሮችን በጥልቀት የመመርመር ፍላጎት መቀነስም ታይቶባቸዋል።
2ኛ. ከመጠን ያለፈ እምነት በሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) መሳሪያዎች ላይ መጣል ሲሆን ጥናቱ የተደረገባቸው ሰዎች ከመሳሪያዉ የሚገኙ ዉጤቶች ላይ ከፍተኛ የሆነ መተማመን እንዳላቸዉ ያሳያል።
ውጤቶቹንም እውነተኛነታቸዉን ለማረጋገጥ ሌላ ተጨማሪ ምንጮችን በማየት ለማረጋገጥ እንደማይሞክሩ ውጤቱ ያመለክታል።
3ኛ. የጥናቱ ውጤት ሰዎች ጥልቅ እና የተወሳሰቡ የሚመስሉ ነገሮችን ከማሰብ እና ምክንያታዊ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ከሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) መሳሪያዎች የሚወጡ ቀላል እና መሰረታዊ ስህተቶችን በማረም ላይ ያተኩራሉ ብሏል።
እንዲሁም የራሳቸዉን አስተሳሰብ በጥቂቱ ስለሚያቀርቡ የግለሰቡን ሀሳብ የማመንጨት ተፈጥሯዊ ብቃቱን እንደሚያሳጣዉ ጥናቱ ይገልጻል።
በጥናቱ መሰረት ከመረጃ ጋር የተያያዙ ስራዎች ከሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) መሳሪያዎች ጥቅም ላይ መዋል በኋላ መረጃን ከመሰብሰብ ወደ ማረጋገጥ መዞራቸውን ያነሳል።
ችግር ፈቺ በሆኑ የሥራ ቦታዎችም ቀጥታ ችግሩን ከመፍታት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምክሮቸን ወደመቀበል ዞረዋል ተብሏል።
በጥናቱ ከተሳተፉ 319 ሰዎች ውስጥ 83 ያህሉ በሰው ሰራሽ አስተውሎት መሳሪያዎች ላይ ያላቸው መተማመን የማገናዘብ አቅማቸውን እንዳዳከመው አምነዋል።
ከዚህ በተጨማሪ 72 ሰዎች ከሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ያገኙት ምላሽ ስህተት እያለው እንኳን ለማረም እንደማይችሉ በጥናቱ ተመላክቷል።
በአጠቃላይ የጥናቱ ማጠቃለያ ሰዎች በስራ ቦታ ላይ ያላቸዉ የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI) መሳሪያዎች አጠቃቀም የሰዎችን ምክንያታዊ የአስተሳሰብ አቅም እየቀነሰዉ መምጣቱን ያሳያል።
ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ተጠቃሚዎች ከሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት መሳሪያዎች በሚመነጩ መልሶች ላይ መተማመናቸው ነው።
በተጨማሪም ከመተንተን ይልቅ ከሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት የሚገኙ ውጤቶችን ወደ ማረጋገጥ ፣ ማቀናጀት እና መሰረታዊ ሰህተቶችን ወደ ማረም መዞራቸው መሆኑን ጥናቱ ያሳያል።
#TikvahEthiopiaFamliyAA
Via @TikvahethMagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
6❤1.28K💔149😭63😱57👏43🙏37🤔34🕊31😢21😡19🥰9