TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ቦትስዋና

ከሰሞኑን በቦትስዋና በተካሄደው ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ መሸነፋቸውን ያመኑት ሞከዌትሲ ማሲሲ ለአዲሱ ተመራጭ ፕሬዜዳንት ዱማ ቦኮ በይፋ በሰላም ፤ አቅፈዋቸውን ስልጣናቸውን አስረክበዋል።

ላለፉት 58 ዓመታት በሥልጣን ላይ የቆየው ' የቦትስዋና ዲሞክራቲክ ፓርቲ ' ህዝቡ በድምጹ ቀጥቶት ከባድ ሽንፈት አስተናግዶ መሪነቱን ተነጥቋል።

ይህ ፓርቲ አፍሪካ ውስጥ ረጅም ዓመታትን በግዢነት የቆየ ነው።

ተቃዋሚ ፓርቲ የነበረው ' አምብሬላ ፎር ዲሞክራቲክ ቼንጅ ' በከፍተኛ ብልጫ በማሸነፍ ፕሬዜዳንታዊ ስልጣኑን ተቆጣጥሯል።

ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት በምርጫ መሸነፋቸውን ካመኑ በኃላ መላው ህዝብ በአንድነት አዲሱን የመንግሥት አስተዳደር እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል።

ቦትስዋና አፍሪካ ውስጥ በተረጋጋ ሰላም እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓቷ በቀዳሚነት ትጠቀሳለች።

#ዴሞክራሲ #ምርጫ

@tikvahethiopia
3.53K👏1.18K🙏158🕊92🥰79😢29😭29😡25🤔20😱18