TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ነዳጅ #ረቂቅአዋጅ

🔴" ዋናው ነገር ኮንትሮባንድ ንግድ መስራታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከባንኮች ብድር መውሰጃ እንደሆነ አረጋግጠናል " - የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት

🔵 " ለኮንትሮባንድ ንግድና ብድር ማግኛ ብሎ የገባው ኩባንያ ስርዓት ይይዛል " - ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር

በህገወጥ የነዳጅ ግብይት የታየዘ ግለሰብ ነዳጁ ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስራትና እስከ 100 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ።

ረቂቁ ምን ይላል ?

- አዲስ የነዳጅ ምርት አከፋፋዮች ስራ ለመጀመር ቢያንስ 500 ሺህ ሊትር የነዳጅ ውጤቶች መያዝ የሚችል ማከማቻ / ዴፖ እና 4 ማደያዎችን ማዘጋጀት እንዳለባቸው ያስገድዳል።

- በስራ ላይ ያሉ ማደያዎች ደግሞ አዋጁ ከሚጸድቅበት ጊዜ ጀምሮ ለአዲስ አከፋፋዮች የተጣሉትን ግዴታዎች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

- አዲስ ጀማሪ ሆኑ ነባሮቹ በ3 ዓመታት ውስጥ ተጨማሪ 6 ማደያዎችን የመገንባት ግዴታ አለባቸው።

- የነዳጅ ውጤቶችን ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ያከማቸ፣ ሊሸጥ ከሚገባው ሰው ቦታና የግብይት ስርዓት ውጭ ሲሸጥ የተገኘ ወይም አደጋ ያስከትላሉ በተባሉ መያዣዎች ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ የተያዘው የነዳጅ ውጤት ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስርና ከብር 50 ሺህ እስከ ብር 100 ሺህ የሚደርስ ቅጣት ይፈጸምበታል።

- መንግሥት ከሚያወጣው የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ተመን ውጪ በተደጋጋሚ የመገበያየት ወንጀል እንዲሁም የነዳጅ ምርቶችን ከባዕድ ነገሮች ጋር መቀላቀል እስከ 3 ዓመት እስርና እስከ 300 ሺህ ብር ቅጣት ያስጥላል።

የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ እስመለአለም ምህረቱ ምን አሉ ?

አሁን አሁን ወደነዳጅ አቅራቢነት ስራ ለመሰማራት ከፍተኛ ፍላጎት እየታየ ነው ብለዋል።

በድርጅቱ በተደረገው ጥናት ይህ ፍላጎት የኮንትሮባንድ ንግድ እና ከባንክ ብድር ለመወሰድ ተብሎ የሚደረግ እንደሆነ ተደርሶበታል ሲሉ ገልጸዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ፥ በዚህ 9 እና 10 ዓመት ውስጥ ከነበሩት 8 ወይም 9 ካምፓኒዎች አሁን 59 መድረሳቸውን ጠቁመዋል።

3ቱ የመንግሥት ገንዘብ አባክነው በፍርድ ቤት ክርክር ላይ ናቸው።

56ቱ ካምፓኒዎችን በማርኬትሼር በመደልደል ነዳጅ እየተሰጠ መሆኑን የገለጹ ሲሆን " ይህ ሁኔታ እራሱ እስካሁን ስምምነት የሌለበት ሁልጊዜ ጭቅጭቅ ያለበት ድርጊት ነው " ብለዋል።

ወደ ነዳጅ ግብይት አዲስ የሚገቡ ካምፓኒዎችን በተመለከተ ምንድነው አላማቸው ? ለምንድነው እንዲህ እያደገ የመጣው የሚለው መጠናቱን ገልጸዋል።

በጥናቱ ውጤትም " ዋናው ነገር ኮንትሮባንድ መስራታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከባንኮች ብድር መውሰጃ እንደሆነ ነው የተረጋገጠው " ብለዋል።

እነዚህ የነዳጅ ካምፓኒዎች ባንኮች ጋር ሄደው ብድር በሚጠይቁበት ጊዜ ባንኮቹ " ከናተ ጋር ያላቸው የሥራ አፈጻጸም ይጻፍልን " እየተባለ ደብዳቤ እንደሚጻፍ ገልጸዋል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ምን አሉ ?

° አዋጁ አላማ መንግሥት በየዓመቱ በሚሊዮን ዶላሮች የሚያወጣበትን ለነዳጅ ምርት በአግባቡ ለማስተዳደር ነው።

° በመንግሥት በኩል የነዳጅ አቅርቦትን የማበራከት አላማ የለም።

° አዋጁ በእያንዳዱ የግብይት ሰንሰለት ውስጥ ባሉት ተዋናዮች ላይ የህግ ሪስትሪክሽኖችን ይጥላል። የአቅራቢ፣ የማደያ ... ግዴታዎች አሉ።

° ግብይታችን ችግር አለበት። የአቅርቦት ችግር ሳይኖር ስርጭት ላይ ትልቅ ችግር አለ። የታሰበላቸው ቦታ ያለመድረስን በተመለከተ በክልሎች የሚቀርበው ቅሬታ ገሚሱ ትክክል ነው።

° ነዳጅ አለ !! ሳምንት ሁለት ሳምንት ገበያ ማስራብ ፣ በነዳጅ ማደያዎች ውስጥ ነዳጅ ይዞ ' ቤንዚን የለም ፤ ናፍጣ የለም ' ብሎ መለጠፍ ይሄ ደግሞ ተጠያቂነት የማያስከትልበት ሴክተራል ባህሪው እንዲቀየር ይታሰባል፤ ይፈለጋል በመንግሥት በኩል ለዛም ነው ይሄ አዋጅ የሚወጣው።

° ከዚህ በኃላ ንግድን አንከለክልም እናሰፋዋለን ፤ ግብይቱ እንዲሳለጥ እንፈልጋለን ነገር ግን ለኮንትሮባንድ ንግድና ብድር ማግኛ ብሎ የገባው ኩባንያ ስርዓት ይይዛል።

° የነዳጅ ኮታ እና ስርጭት ላይ ፍትሃዊ ስርዓት ለመፍጠር ይሰራል።

° ከአቅርቦት እና ስርጭት ይልቅ ማስተዳደሩ ከባድ ነው።

° ነዳጅ እያላቸው ዘግተው የሚቀመጡ ማደያዎች በስፋት አሉ። የቅጣት መጠኑ ላይ ጠንካራ ስራ ይሰራል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከሪፖርተር እንዲሁም ከህ/ተ/ም/ቤት የቀጥታ ስርጭት ማግኘቱን ይገልጻል።

#ኢትዮጵያ #ነዳጅ #ረቂቅአዋጅ

@tikvahethiopia
564👏215😡74😭66🙏41🕊39😢22🤔18😱17🥰8
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኢትዮጵያ #ረቂቅአዋጅ

የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ መሬትን በሊዝ በባለቤትነት መያዝ የሚያስችላቸው የአዋጅ ረቂቅ ነገ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባል።

የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት " ባለቤት ' ወይም  " ባለይዞታ " የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣው ይህ " የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበት " ወይም " ለመኖሪያ ቤት ግንባታ የሚውል መሬት የሚያገኙበትን " ህጋዊ አሰራር ለመዘርጋት ነው።

ረቂቅ አዋጁ ምን ይላል ?

- ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው ግለሰቦች በኢትዮጵያ መሬትን፣ የመኖሪያ ቤትን ወይም ተያያዥ ግንባታዎችን በባለቤትነት ለመያዝ፤ ቢያንስ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ሊመድቡ እንደሚገባ ይደነግጋል።

- በውጭ ዜጋ " በሊዝ ባለይዞታነት " ወይም " ባለቤትነት " የሚያዝ መሬት ወይም የመኖሪያ ቤት፤ " የማይንቀሳቀስ ንብረት " ተደርጎ ይወሰዳል። " ሊዝ "  ማለት " አግባብነት ባለው ህግ መሰረት በጊዜ በተገደበ ውል ለመኖሪያ ቤት ግንባታ ዓላማ የሚውል የከተማ ወይም የገጠር መሬት የሚገኝበት የመሬት ይዞታ ስሪት " ነው።

- ማንኛውም የውጭ ዜጋ በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ ሊሆን የሚችለው በአዋጁ የተዘረዘሩ ቅደመ ሁኔታዎችን ሲያሟላ ነው።

እነዚህም ፦
° የውጭ ዜጋው ስም፣ ዜግነት እና ሌሎችን ማንነትን የሚገልጹ ህጋዊ ሰነዶችን ማቅረብ አለበት።
° የውጭ ዜጋው የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለመብት ለመሆን የሚያስፈልግ አነስተኛ የገንዘብ መጠን ለማሟላት የሚያስችል በቂ አቅም ያለው መሆን አለበት።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ለመሆን፤ የሊዝ ዋጋውን ጨምሮ ለአንድ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሙሉ ዋጋ ወይም ለመኖሪያ ቤት ግዢ የሚመድበው አነስተኛ የገንዘብ መጠን ከ150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ያነሰ ሊሆን አይችልም።
° የውጭ ዜጋው የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆን ይገባዋል።

እነዚህን መስፈርቶች የሚያሟላ አንድ የውጭ ዜጋ ከከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የሚሰጥ ፈቃድ ሊያገኝ ይገባዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ " የፈቃድ ይሰጠኝ " ማመልከቻ ላቀረበ የውጭ ዜጋ፤ አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ በ15 ቀናት ውስጥ ውሳኔ መስጠት ይጠበቅበታል።

- የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከውጭ ዜጎች የሚጠበቀውን የአነስተኛ ገንዘብ መጠን ከፍ ወይም ዝቅ የሚያደርግ የእያንዳንዱን የሊዝ ቦታ ወይም ቤት ስፋት እንዲሁም የሊዝ ይዞታዎችን ወይም ቤቶችን አጠቃላይ ቁጥር የሚወስን መመሪያ የማውጣት ስልጣን በአዋጅ ረቂቁ ተሰጥቶታል። መመሪያውን የሚያወጣው፤ የቤቶች ገበያ ወቅታዊ ሁኔታን፣ የከተሞች የማይንቀሳቀስ ንብረት አማካይ ዋጋን፣ የውጭ ዜጎች በቤቶች ገበያ ያላቸውን የተሳትፎ መጠን እና የአዋጁን ዓላማ ለማሳካት የሚረዱ ሌሎች ምክንያቶችን መሰረት በማድረግ ነው።

- የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ፤ የተወሰኑ ሀገራት ዜጎችን ወይም ዜግነት የሌላቸው የውጭ ሀገር ሰዎችን በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ እንዳይሆኑ #ሊከልክል ይችላል።

- ለውጭ ዜጎች የተገደቡ ልዩ ቦታዎች እና የድንበር አካባቢዎችም እንዲሁ በሚያወጣ መመሪያ ይወሰናሉ።

- በውጭ ዜጎች ላይ የተጣሉ ሌሎች ገደቦችም አሉ።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ ለመሆን ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋም ወይም ምንጭ ገንዘብ መበደር ወይም ካፒታል ማሰባሰብ አይችልም።
° የውጭ ዜጎች ይህን ጉዳይ ለማስፈጸም የሚያስፈልጉ የሊዝ፣ የቤት ግዢ፣ የግንባታ ፈቃድ ወይም ተያያዥ የመንግስታዊ አገልግሎት ክፍያዎችን መክፈል ያለባቸው በኢትዮጵያ ተቀባይነት ባለው የውጭ ምንዛሬ ብቻ ነው።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ በመንግስት ቀጥተኛ ድጎማ ለዜጎች በሚሰሩ የጋራ መኖሪያ ህንጻዎች ውስጥ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት መሆን አይችልም። ይህ ገደብ በግል እና በመንግስት አጋርነት ወይም በተመሳሳይ የቤቶች ልማት ማዕቀፍ በፌደራል ወይም በክልል መንግስታት የሚገነቡ መኖሪያ ቤቶችን አያካትትም። ለውጭ ዜጎች የተቀመጠው ገደብ በእነዚህ አካላት አማካኝነት ለትርፍ ዓላማ ተገንብተው ለሽያጭ የሚቀርቡ ቤቶች ላይ ተፈጻሚ አይሆንም።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።

@tikvahethiopia
😡1.28K209😭88🤔72💔41🙏32👏21🕊18😢17😱10🥰7