🔊 #የሰራተኞችድምጽ
🔴 " ቅሬታችን በአስቸኳይ ምላሽ ያግኝ " - የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሰራተኞች
⚫️ " ለክልሉ መንግስት ቅሬታውን አቅርበናል። ነገር ግን ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ መስጠት አልቻለም " - የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የሰው ኃብት አስተዳደር
የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሰራተኞች " በሀገር አቀፍ ደረጃ ጥቅምት አንድ ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ጭማሪ እስካሁን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ተግባራዊ ባለማድረጉ ለከፋ ችግር ተጋልጠናል " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።
በተጨማሪ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሸን ለሁሉም ሲቪል ሰርቫንት የኑሮ ውድነት መደጎሚያ ያደረገውን ጭማሪ እስካሁን አልተጨመረንም ብለዋል።
ሰራተኞቹ የተለያዩ ጥያቄዎችን ለክልሉ ገቢዎች ቢሮ ማቅረባቸውን የገለፁ ሲሆን ጥያቄያችን በቀጠሮ የታጀበ የአመታት ችግር ሆኖ ቀጥሏል ብለዋል።
" የክልሉ መንግስት የተቋሙን ሰራተኞች ድካም እና መስዋዕትነት የተረዳው አይመስለንም። እኛ ተስፋ ቆርጠናል ፣ የሚሰማን አካል የለም፣ እየታገትን እና እየተገደልን ነው ፣ ከማህበራዊ ሂወት ተገለናል " ብለዋል።
አክለውም " እንደሰው መቆጠር ናፍቆናል ፣ ችግሮቻችን በዝተዋል ፣ ችግሮችን የሚፈታልን የለም ፣ እባካችሁ የሚሰማን አካል ካለ የሁለት አመት ቅሬታችን ይሰማ " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
አያይዘውም ሰራተኞቹ መጋቢት 5 / 2015 ዓ.ም " ይወክሉናል " ያሏቸውን ተወካዮች በመምረጥ ለክልሉ ገቢዎች ቢሮ ፣ ለበጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና ለብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አመራር እንዲሁም ለርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ ቅሬታቸውን እንዳቀረቡ ገልፀዋል።
ሰራተኞቹ በሰዓቱ ለአመራሮቹ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች በርካታ መሆናቸውን የገልፁ ሲሆን ከጥያቄዎቻቸው መካከል ፦
- የገቢ ተቋሙ ሰራተኛ በልዩ ሁኔታ በጥናት ላይ የተመሰረተ ልዩ ጥቅማጥቅም ይደረግልን፣
- የእርከን ጭማሪ በአደረጃጃትና በመመሪያ ደረጃ የወረደ ቢሆንም በአፈጻጸም ተግባራዊ ይደረግ
- የሰራተኛውን ጥቅም የሚመለከት ጥናት ሲጠና እስከ ታችኛዉ መዋቅር ያለ ባለሙያ ተሳታፊ ይደረግ የሚሉ እና መሰል ጥያቄዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በመሆኑም በሰዓቱ አመራሮቹ በምላሻቸው ጥያቄው " ተገቢነት ያለው የባለሙያውን ሮሮና ብሶት ያዘለ ስለሆነ በቀጣይ የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ ይህንን አካል የግድ ማትጋትና ማበረታታት አስፈላጊ ስለሆነ ጥያቄውን እንፈታለን " ብለውን ነበር ሲሉ አስታውሰዋል።
" ይሁን እንጂ ቅሬታችንን ሰምቶ የፈታልን አካል የለም " ያሉ ሲሆን " አሁንም ለከፋ ችግር ተጋልጠን እንገኛለን " ሲሉ አክለዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ሰራተኞቹ የክልሉን የገቢዎች ቢሮ የሰው ሀብት አስተዳደር ቅሬታችንን ፍቱልን ብለን ጠይቀን ነበር ያሉ ሲሆን ሀላፊውም " ቅሬታችሁ ከአቅማችን በላይ ነው። በአስቸኳይ ምላሽ ይሰጣቸው ስንል ለክልሉ መንግስት ጥያቄ አቅርበናል እስካሁን ግን መልስ የለም " የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።
እንደተቋም በቀን እስከ 200 ሚሊየን ገቢ የሚሰበስብ ሰራተኛ አንድ ቀን ስራ ቢያቆም እንኳ ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመት ቀላል መሆኑን ጠቁመዋል።
ከቅሬታ አቅራቢዎቹ መካከል አንደኛው ከደሴ ኮምቦልቻ የደወለልን ባለሙያ ነው።
" ስራችን ከማህበረሰቡ ሂወት ነጥሎናል፣ ከነጋዴዎች አራርቆናል፣ ደመወዝ ሲያልቅብን እንኳ ከነጋዴዎች መበደር አንችልም፣ ቤት ለመከራየት ስንጠይቅ ገቢዎች ቢሮ ከሆነ የምትሰሩት አናከራይም እያሉን ነው፣ አሁን ላይ ችግሮችን መቋቋም አቅቶናል " ሲል ተናግሯል።
ስሙን መጥቀስ ያልፈለገው የደባርቅ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ሰራተኛ ደግሞ " የደረጃ እርከን እየተሰራልን አይደለም 2012 ዓ.ም የደመወዝ ጭማሪ እንደተደረገ እስካሁን አልተጨመረንም ፤ በስራ አጋጣሚ ሂወታቸውን የገበሩ ጓዶች አሉ የክልሉን መንግስት ታግሰናል አሁን ላይ ግን ኑሮ ከብዶናል " ሲል ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም የሰራተኞቹን ቅሬታ በመቀበል ለአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የሰው ሃብት አስተዳደር ሀላፊ ለአቶ ሽመልስ አዱኛ ቅሬታቸውን ያቀረበ ሲሆን እርሳቸውም ምላሽ ያሉትን ሰጥተዋል።
" የሰራተኞቹ ቅሬታ ተገቢ ነው። በኛ በኩል ቅሬታውን እናውቃለን ። ለክልሉ መንግስት ቅሬታውን አቅርበናል። ነገር ግን ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ መስጠት አልቻለም በዚህ ጉዳይ የተለየ መረጃ ልሰጥ አልችልም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የባለሙያዎችን ቅሬታ በተመለከተ የክልሉን መንግስት እና የኮሚኒኬሽን ባለሙያ እንዲሁም የክልሉን ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ በስልክ አግኝቶ ምላሻቸውን ለማካተት ያደረገው ጥረት ባለመሳካቱ ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም።
በመጨረሻም ሰራተኞቹ " ቅሬታችን በአስቸኳይ ምላሽ የማያገኝ ከሆነ ከየካቲት 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ስራ የምናቆም መሆኑን እንገልፃለን " ብለዋል።
(ቲክቫህ ጉዳዩን እስከመጨረሻው ተከታትሎ መረጃውን የሚያደርሳችሁ ይሆናል )
#TikvahEthiopia
@tikvahethmagazine
🔴 " ቅሬታችን በአስቸኳይ ምላሽ ያግኝ " - የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሰራተኞች
⚫️ " ለክልሉ መንግስት ቅሬታውን አቅርበናል። ነገር ግን ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ መስጠት አልቻለም " - የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የሰው ኃብት አስተዳደር
የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሰራተኞች " በሀገር አቀፍ ደረጃ ጥቅምት አንድ ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ጭማሪ እስካሁን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ተግባራዊ ባለማድረጉ ለከፋ ችግር ተጋልጠናል " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።
በተጨማሪ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሸን ለሁሉም ሲቪል ሰርቫንት የኑሮ ውድነት መደጎሚያ ያደረገውን ጭማሪ እስካሁን አልተጨመረንም ብለዋል።
ሰራተኞቹ የተለያዩ ጥያቄዎችን ለክልሉ ገቢዎች ቢሮ ማቅረባቸውን የገለፁ ሲሆን ጥያቄያችን በቀጠሮ የታጀበ የአመታት ችግር ሆኖ ቀጥሏል ብለዋል።
" የክልሉ መንግስት የተቋሙን ሰራተኞች ድካም እና መስዋዕትነት የተረዳው አይመስለንም። እኛ ተስፋ ቆርጠናል ፣ የሚሰማን አካል የለም፣ እየታገትን እና እየተገደልን ነው ፣ ከማህበራዊ ሂወት ተገለናል " ብለዋል።
አክለውም " እንደሰው መቆጠር ናፍቆናል ፣ ችግሮቻችን በዝተዋል ፣ ችግሮችን የሚፈታልን የለም ፣ እባካችሁ የሚሰማን አካል ካለ የሁለት አመት ቅሬታችን ይሰማ " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
አያይዘውም ሰራተኞቹ መጋቢት 5 / 2015 ዓ.ም " ይወክሉናል " ያሏቸውን ተወካዮች በመምረጥ ለክልሉ ገቢዎች ቢሮ ፣ ለበጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና ለብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አመራር እንዲሁም ለርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ ቅሬታቸውን እንዳቀረቡ ገልፀዋል።
ሰራተኞቹ በሰዓቱ ለአመራሮቹ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች በርካታ መሆናቸውን የገልፁ ሲሆን ከጥያቄዎቻቸው መካከል ፦
- የገቢ ተቋሙ ሰራተኛ በልዩ ሁኔታ በጥናት ላይ የተመሰረተ ልዩ ጥቅማጥቅም ይደረግልን፣
- የእርከን ጭማሪ በአደረጃጃትና በመመሪያ ደረጃ የወረደ ቢሆንም በአፈጻጸም ተግባራዊ ይደረግ
- የሰራተኛውን ጥቅም የሚመለከት ጥናት ሲጠና እስከ ታችኛዉ መዋቅር ያለ ባለሙያ ተሳታፊ ይደረግ የሚሉ እና መሰል ጥያቄዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በመሆኑም በሰዓቱ አመራሮቹ በምላሻቸው ጥያቄው " ተገቢነት ያለው የባለሙያውን ሮሮና ብሶት ያዘለ ስለሆነ በቀጣይ የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ ይህንን አካል የግድ ማትጋትና ማበረታታት አስፈላጊ ስለሆነ ጥያቄውን እንፈታለን " ብለውን ነበር ሲሉ አስታውሰዋል።
" ይሁን እንጂ ቅሬታችንን ሰምቶ የፈታልን አካል የለም " ያሉ ሲሆን " አሁንም ለከፋ ችግር ተጋልጠን እንገኛለን " ሲሉ አክለዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ሰራተኞቹ የክልሉን የገቢዎች ቢሮ የሰው ሀብት አስተዳደር ቅሬታችንን ፍቱልን ብለን ጠይቀን ነበር ያሉ ሲሆን ሀላፊውም " ቅሬታችሁ ከአቅማችን በላይ ነው። በአስቸኳይ ምላሽ ይሰጣቸው ስንል ለክልሉ መንግስት ጥያቄ አቅርበናል እስካሁን ግን መልስ የለም " የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።
እንደተቋም በቀን እስከ 200 ሚሊየን ገቢ የሚሰበስብ ሰራተኛ አንድ ቀን ስራ ቢያቆም እንኳ ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመት ቀላል መሆኑን ጠቁመዋል።
ከቅሬታ አቅራቢዎቹ መካከል አንደኛው ከደሴ ኮምቦልቻ የደወለልን ባለሙያ ነው።
" ስራችን ከማህበረሰቡ ሂወት ነጥሎናል፣ ከነጋዴዎች አራርቆናል፣ ደመወዝ ሲያልቅብን እንኳ ከነጋዴዎች መበደር አንችልም፣ ቤት ለመከራየት ስንጠይቅ ገቢዎች ቢሮ ከሆነ የምትሰሩት አናከራይም እያሉን ነው፣ አሁን ላይ ችግሮችን መቋቋም አቅቶናል " ሲል ተናግሯል።
ስሙን መጥቀስ ያልፈለገው የደባርቅ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ሰራተኛ ደግሞ " የደረጃ እርከን እየተሰራልን አይደለም 2012 ዓ.ም የደመወዝ ጭማሪ እንደተደረገ እስካሁን አልተጨመረንም ፤ በስራ አጋጣሚ ሂወታቸውን የገበሩ ጓዶች አሉ የክልሉን መንግስት ታግሰናል አሁን ላይ ግን ኑሮ ከብዶናል " ሲል ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም የሰራተኞቹን ቅሬታ በመቀበል ለአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የሰው ሃብት አስተዳደር ሀላፊ ለአቶ ሽመልስ አዱኛ ቅሬታቸውን ያቀረበ ሲሆን እርሳቸውም ምላሽ ያሉትን ሰጥተዋል።
" የሰራተኞቹ ቅሬታ ተገቢ ነው። በኛ በኩል ቅሬታውን እናውቃለን ። ለክልሉ መንግስት ቅሬታውን አቅርበናል። ነገር ግን ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ መስጠት አልቻለም በዚህ ጉዳይ የተለየ መረጃ ልሰጥ አልችልም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የባለሙያዎችን ቅሬታ በተመለከተ የክልሉን መንግስት እና የኮሚኒኬሽን ባለሙያ እንዲሁም የክልሉን ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ በስልክ አግኝቶ ምላሻቸውን ለማካተት ያደረገው ጥረት ባለመሳካቱ ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም።
በመጨረሻም ሰራተኞቹ " ቅሬታችን በአስቸኳይ ምላሽ የማያገኝ ከሆነ ከየካቲት 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ስራ የምናቆም መሆኑን እንገልፃለን " ብለዋል።
(ቲክቫህ ጉዳዩን እስከመጨረሻው ተከታትሎ መረጃውን የሚያደርሳችሁ ይሆናል )
#TikvahEthiopia
@tikvahethmagazine
❤146🤔31😭21🙏14🕊10😡8🥰4😢3
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake ትላንት ለሊት 9:52 ላይ በርካቶችን ከተኙበት የቀሰቀሰው በሬክተር ስኬል 5.8 ከተለካው የመሬት መንቀጥቀጥ በኃላ በሬክተር ስኬል 4.4 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር መረጃ መለዋወጣችን ይታወሳል። ዛሬ ደግሞ በሬክተር ስኬል ፦ ➡️ 4.7 ➡️ 4.6 ➡️ በድጋሚ 4.7 ➡️ በድጋሚ 4.6 ➡️ 4.9 የተለኩ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች ተመዝግበዋል። ሁሉም…
" ሰራተኞቹ ከስራ የተሰናበቱበት መንገድ ከህግ ውጭ በመሆኑ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ እንቅስቃሴ ተጀምሯል " - የሰራተኞች ማህበር ሊቀ መንበር
በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ጉዳት የደረሰበት የከሰም ስኳር ፋብሪካ ከ1 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰራተኞቹን የ2 ወር ማስጠንቀቂያ በመስጠት የሥራ ውላቸው እንዲቋረጥ ማድረጉ ቅሬታ አስነስቷል።
ስሜ እንዳይጠቀስ ያሉን አንድ ሰራተኛ በአሁኑ ሰዓት ሰራተኞቹ በመጠለያ ጣቢያና ከዘመድ ጋር ተጠግተው እንደሚገኙ ገልጸው ለሁለት ወራት ያህል ደመወዝ ባለመከፈሉ በከፋ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
የከሰም ስኳር ፈብሪካ የሰራተኞች ማኅበር ሊቀ መንበር አቶ ጌታሁን አርፊጮ በበኩላቸው ፈብሪካው ሰራተኞችን ከስራ ያሰናበተበት መንገድ ከህግ አግባብ ውጭ በመሆኑ ጉዳዩን ወደ ፍ/ቤት ለመውሰድ እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል።
የከሰም ስኳር ፈብሪካ የሰራተኞች ማኅበር ሊቀ መንበር አቶ ጌታሁን በዝርዝር ምን አሉ ?
" ፋብሪካው ሰራተኞችን ሲያሰናብት የሁለት ወር ማስጠንቀቂያ ማለትም ሚያዚያ 10/2017 ዓ.ም የሚያበቃ ውል በመስጠት ነው።
ይህ ደግሞ ትክክል አይደለም በመጀመሪያ ሰራተኞችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከመበተን አማራጮችን መመልከት ነበረበት።
በአማራጭነትም ወደ ሌሎች መስሪያ ቤቶች አዘዋውሮ ማሰራት ወይም እዛው ግቢ ውስጥ ምርት ሊሰጡ የሚችሉ ሰብሎችን እያመረቱ እንዲቆዩ ማድረግ ይችል ነበር።
ፋብሪካው ለወጭ ቅነሳ ሲል የሰራተኞችን ጥቅም አሳጥቷል መብትም ጥሷል። ሰራተኞቹ በሁለት ወር የማስጠንቀቂያ ጊዜ ከሰጠ በኃላ 1 ወር ከ14 ቀን ወደ ኃላ ተመልሰው የዓመት እረፍት እንዲሞሉ አስገድዷቸዋል።
ይህም ትልቅ የመብት ጥሰት ነው። በዚህ ወቅት ስራ ላይ ነበሩ ደሞዝም በልተውበታል ይህንን አናደርግም ያሉ ሰራተኞች በቅርብ አለቆቻቸው በግዳጅ የአመት እረፍት እንዲሞሉ ተደርገዋል።
ይህ የሆነበት ምክንያትም ሰራተኛው የዓመት እረፍቱን በገንዘብ እንዳይጠይቅ ለማድረግ ታስቦ ነው።
ሴት ሰራተኞችን በተመለከተ በአሰሪ ሰራተኛ አዋጅና በህብረት ስምምነቱ መሰረት ነፍሰጡር በሆኑበት ሰዓትና ወልደው አራት ወር እስኪሞላቸው ድረስ ከስራ አይቀነሱም ይላል ይህ ህግ ግን ተጥሷል።
ማስጠንቀቂያ አሰጣጡም ህግን የተከተለ አይደለም። በአሰሪና ሰራተኛ አዋጁ መሰረት አንድ ዓመት ያገለገለ የ 1 ወር ማስጠንቀቂያ ይኖረዋል።
እስከ 9 አመት ላገለገለ 2 ወር ከ9 አመት በላይ ላገለገል 3 ወር የማስጠንቀቂያ ይሰጠው ነበር ፋብሪካው ግን ይህንን አላደረገም።
ፋብሪካው የሰራተኞችን ቅነሳ ሲሰራ ከሰራተኛ ማኅበሩ ጋር መነጋገር ሲገባው ብቻውን ወስኖ ሰራተኞቹን አሰናብቷል፤ ይህንን የመብት ጥሰት በመያዝ ወደ ህግ ለመሄድ እንቅስቃሴ ተጀምሯል " ብለዋል።
ሊቀመንበሩ እነዚህንና ሌሎች ጥያቄዎችን በመያዝ ለአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር ቢሮ ፤ ለኢትዮጵያ ኢንቭስትመንት ሆልዲንግ፤ ለከሰም ስኳር ፈብሪካ አመራር ቦርድ ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ነገር ግን ምላሽ የሚሰጣቸው አካል አንዳላገኙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም የከሰም ስኳር ፋብሪካ ስራ አስኪያጅን አቶ አሊ ሁሴን ለማግኘት ያደረገው ጥረት ስልኩ ባለማንሳታቸው አስተያየታቸውን ማካተት ለጊዜው አልቻለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተቋሙ በኩል ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑን ይገልጻል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤177💔45😢19🕊19😡19😭15🤔7🥰5