" ነበሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን ይቀጥላል " - የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
በኢትዮጵያ የተመረተ አዲስ ፓስፖርት ዛሬ ይፋ ሆኗል።
ፓስፖርቱ የግለሰቡን ባዮግራፊክ መረጃ ብቻ ሳይሆን የጣት ዐሻራ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ አለው ተብሏል።
በኢትዮጵያ ውስጥ የሚመረተው ይህ ፓስፖርት፤ የቪዛ ገጾቹ የኢትዮጵያን መልክ የያዙ መሆናቸው ተጠቅሷል።
ይህም ከዚህ ቀደም በውጭ ሀገር አምራች ድርጅት እጅ የነበረውን ዲዛይን ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት እንዲሸፈን አድርጓል ተብሏል።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በአዲስ የዘርጋው የኢ-ፓስፖርት ሲስተም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስና በጃፓኑ ቶፓን ሴኩሪቲ ኢትዮጵያ አ.ማ. አማካይነት የተሰራ ነው።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፤ ነበሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን የሚቀጥል ሲሆን የዕድሳት ጊዜው ሲደርስ በኢ-ፓስፖርት ይተካል ተብሏል።
አገልግሎት መ/ቤቱ ፤ " 14 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈትም አገልግሎቱን ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቋል " ያለ ሲሆን " ከአንድ ነጥብ 5 ሚልየን በላይ ኢ-ፓስፖርት ታትሞ ተዘጋጅቷል " ሲል ገልጿል።
አዲሱ የኢ-ፓስፖርት በነበረው ዋጋ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እንደሚሆን የተነገረ ሲሆን ደንበኞች ባሉበት ፓስፖርታቸውን በፍጥነት ማግኘት እንዲችሉ ያደርጋል ተብሏል።
" አዲሱን ኢ-ፓስፖርት በሁለት ወር ከ10 ቀን ማግኘት ይቻላል " ሲል አገልግሎቱ አሳውቋል።
የፓስፖርቱ አገልግሎት ጊዜ 10 ዓመት ሲሆን የዜጎችን ጊዜ፣ ገንዘብ እና ጉልበት ይቆጥባል ተብሏል።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊ ዳዊት ፥ " አዲሱ ኢ-ፓስፖርት እስከአሁን ኢትዮጵያ ካላት ፓስፖርት በአይነቱና በደረጃው እጅግ ከፍ ባለ ጥረት የተዘጋጀ የጉዞ ሰነድ ነው " ብለዋል።
#EPA #ICS
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ የተመረተ አዲስ ፓስፖርት ዛሬ ይፋ ሆኗል።
ፓስፖርቱ የግለሰቡን ባዮግራፊክ መረጃ ብቻ ሳይሆን የጣት ዐሻራ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ አለው ተብሏል።
በኢትዮጵያ ውስጥ የሚመረተው ይህ ፓስፖርት፤ የቪዛ ገጾቹ የኢትዮጵያን መልክ የያዙ መሆናቸው ተጠቅሷል።
ይህም ከዚህ ቀደም በውጭ ሀገር አምራች ድርጅት እጅ የነበረውን ዲዛይን ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት እንዲሸፈን አድርጓል ተብሏል።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በአዲስ የዘርጋው የኢ-ፓስፖርት ሲስተም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስና በጃፓኑ ቶፓን ሴኩሪቲ ኢትዮጵያ አ.ማ. አማካይነት የተሰራ ነው።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፤ ነበሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን የሚቀጥል ሲሆን የዕድሳት ጊዜው ሲደርስ በኢ-ፓስፖርት ይተካል ተብሏል።
አገልግሎት መ/ቤቱ ፤ " 14 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈትም አገልግሎቱን ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቋል " ያለ ሲሆን " ከአንድ ነጥብ 5 ሚልየን በላይ ኢ-ፓስፖርት ታትሞ ተዘጋጅቷል " ሲል ገልጿል።
አዲሱ የኢ-ፓስፖርት በነበረው ዋጋ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እንደሚሆን የተነገረ ሲሆን ደንበኞች ባሉበት ፓስፖርታቸውን በፍጥነት ማግኘት እንዲችሉ ያደርጋል ተብሏል።
" አዲሱን ኢ-ፓስፖርት በሁለት ወር ከ10 ቀን ማግኘት ይቻላል " ሲል አገልግሎቱ አሳውቋል።
የፓስፖርቱ አገልግሎት ጊዜ 10 ዓመት ሲሆን የዜጎችን ጊዜ፣ ገንዘብ እና ጉልበት ይቆጥባል ተብሏል።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊ ዳዊት ፥ " አዲሱ ኢ-ፓስፖርት እስከአሁን ኢትዮጵያ ካላት ፓስፖርት በአይነቱና በደረጃው እጅግ ከፍ ባለ ጥረት የተዘጋጀ የጉዞ ሰነድ ነው " ብለዋል።
#EPA #ICS
@tikvahethiopia
👏1.6K❤262😡255🙏71😭67🤔47🕊39😱29🥰28😢12
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Passport
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለአዲስ አበባ አስቸኳይ ፓስፖርት አመልካቾች ባሰራጨው መልዕክት የአስቸኳይ ፖስፖርት ኦንላይን ሲስተም የተወሰነ ማሻሻያ ተደርጎበት ስራ መጀመሩን ገልጿል።
ከግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ሁሉም አመልካች በኦንላይን በማመልከት በቀጠሮ ቀኑ ብቻ ወደ ተቋሙ መሄድ መስተናገድ እንደሚችል አሳውቋል።
በኦን ላይን መሙላት ያልቻሉ አስቸኳይ ጉዳይ ያላቸው አመልካቾች በአካል መጥተው መስተናገድ እንደሚችሉ ገልጿል።
በተጨማሪ አገልግሎቱ ፥ " ከግንቦት 6/ 2017 ዓ/ም ጀምሮ መደበኛ የፓስፖርት አገልግሎት ከጠዋቱ 12:00 - 8:00 ሰአት ድረስ የአስቸኳይ ፓስፖርት አገልግሎት ደግሞ ከ9:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 4:00 ሰአት በሁለት ፈረቃ እንሰጣለን በቀጠሮ ቀናችሁ በፕሮግራሙ መሰረት ወደተቋማችን በመምጣት ተስተናገዱ " ብሏል።
" ከቀጠሮ ቀን ውጭ በተቋሙ አካባቢ መቆምም ሆነ አላስፈላጊ እንቅስቃሴ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ነው " ሲልም አሳስቧል።
#ICS
@tikvahethiopia
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለአዲስ አበባ አስቸኳይ ፓስፖርት አመልካቾች ባሰራጨው መልዕክት የአስቸኳይ ፖስፖርት ኦንላይን ሲስተም የተወሰነ ማሻሻያ ተደርጎበት ስራ መጀመሩን ገልጿል።
ከግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ሁሉም አመልካች በኦንላይን በማመልከት በቀጠሮ ቀኑ ብቻ ወደ ተቋሙ መሄድ መስተናገድ እንደሚችል አሳውቋል።
በኦን ላይን መሙላት ያልቻሉ አስቸኳይ ጉዳይ ያላቸው አመልካቾች በአካል መጥተው መስተናገድ እንደሚችሉ ገልጿል።
በተጨማሪ አገልግሎቱ ፥ " ከግንቦት 6/ 2017 ዓ/ም ጀምሮ መደበኛ የፓስፖርት አገልግሎት ከጠዋቱ 12:00 - 8:00 ሰአት ድረስ የአስቸኳይ ፓስፖርት አገልግሎት ደግሞ ከ9:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 4:00 ሰአት በሁለት ፈረቃ እንሰጣለን በቀጠሮ ቀናችሁ በፕሮግራሙ መሰረት ወደተቋማችን በመምጣት ተስተናገዱ " ብሏል።
" ከቀጠሮ ቀን ውጭ በተቋሙ አካባቢ መቆምም ሆነ አላስፈላጊ እንቅስቃሴ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ነው " ሲልም አሳስቧል።
#ICS
@tikvahethiopia
👏367❤100😡61🙏31😢21🕊13😭12🤔10🥰2😱2