TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ማስታወሻ : መንገዶቹ ተዘግተዋል።

በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ከሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ጋር በተያያዘ ከላይ በምስሉ የተዘረዘሩት መንገዶች ከዚህ ሰዓት አንስቶ ተዘግተዋል።

ከቤት ለስራም ይሁን ለሌላ ጉዳይ የወጣችሁ አማራጭ መንገዶችን ተጠቀሙ።

@tikvahethiopia
🙏649😡144120🥰69👏40🕊26😭20🤔13😢11😱7
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ማስታወሻ #የኢትዮጵያአየርመንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በTRAINEE CABIN CREW ፣ በSENIOR ACCOUNTANT I እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ማስታወቂያ አውጥቷል።

ለTRAINEE CABIN CREW በኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ (ዝቅተኛው) 200 ነጥብ ያስመዘገበ ለማመልከት ብቁ ነው።

የዕድሜ ገደቡ ከ19 እስከ 30 ዓመት ነው።

ቁመት ቢያንስ 1.58 ሜትር እና 212 ሴ.ሜ የሆነ ክንድ ለሴት እንዲሁም ለወንድ ቢያንስ 1.70 ሜትር ቁመት መሆን አለበት።

ምዝገባ የተጀመረ ሲሆን እስከ ህዳር 12/2017 ዓ/ም ድረስ ይቆያል።

ምዝገባው ፦
- በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ)
- አዲስ አበባ (በኦንላይን ልክ ማመልከቻው ሲከፈት ይፋ ይደረጋል)
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ (አምቦ)
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ (አርባ ምንጭ)
- አሶሳ ዩኒቨርሲቲ (አሶሳ)
- ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ባህር ዳር)
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ (ደሴ)
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ (ድሬዳዋ)
- ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ( ጋምቤላ)
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ጎንደር)
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ (ሀዋሳ)
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ (ጅግጅጋ)
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ (ጅማ)
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ (መቐለ)
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ)
- መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ (ሮቤ)
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ (ሰመራ)
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ (ወልቂጤ) ይከናወናል።

ተጨማሪ መረጃዎች ለማግኘት እና ለማመልከት 👇
https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies

@tikvahethiopia
244👏45😭24😡21🤔15🙏12🥰11😢10🕊3😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥቆማ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ጥሪ ማስታወቂያ አውጥቷል። ኢትዮጵያ በቀጣይ የካቲት ወር በአፍሪካ ህብረት ጉባኤ የሚሳተፉ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት እያደረገች ነው። የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከአቀባበል እስከ አሸኛኘት ባለው የመስተንግዶ መርሃግብር በጎ ፍቃደኛ ፕሮቶኮል ካዴቶችን በመቀበል አሰልጥኖ በተለያዩ የፕሮቶኮል ሥራዎች ላይ ማሰማራት እንደሚፈልግ ገልጿል።…
#ማስታወሻ

ምዝገባው ዛሬ ተጀምሯል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለመስጠት ፍላጎት ያላቸውን ዜጎች ዛሬ መመዝገብ ጀምሯል።

ኢትዮጵያ በቀጣይ የካቲት ወር በአፍሪካ ህብረት ጉባኤ የሚሳተፉ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት እያደረገች ነው።

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከአቀባበል እስከ አሸኛኘት ባለው የመስተንግዶ መርሃግብር በጎ ፍቃደኛ ፕሮቶኮል ካዴቶችን በመቀበል አሰልጥኖ በተለያዩ የፕሮቶኮል ሥራዎች ላይ ማሰማራት እንደሚፈልግ ገልጿል።

በመሆኑም ፦
- የእንግሊዘኛ፣
- የፈረንሳይኛ
- የዓረብኛ ቋንቋዎችን መናገርና መጻፍ የሚችሉ እና ዕድሚያቸው ከ18-30 የሆነ ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ከዛሬ ጀምሮ ለ5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ መመዝገብ ይችላሉ።

ምዝገባው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋናው መ/ቤት በአካል በመገኘት ነው የሚከናወነው።

ተመዝጋቢዎች ለምዝገባ ሲመጡ የትምህርት ማስረጃቸውንና ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ ይዘው መቅረብ አለባቸው።

ተጨማሪ መረጃዎችን ደግሞ በስልክ ቁጥር +251911210234 / +251912663737 ላይ ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።

@tikvahethiopia
175😡72👏24🤔16🙏15🕊4😭4😢3🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
#መቄዶንያ “ ህንፃው ለማጠናቀቅ ገንዘብ ተቸግረናል። ለማጠናቀቅ ወደ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልገናል ” - መቄዶንያ መቄዶንያ የአረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በሚያስገነባው ሆስፒታል ጭምር ያለው ህንፃ ለማጠናቀቅ የገንዘብ እጥረት ስለገጠመው እርዳታ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበ። ከየካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ “ በሰይፉ ኢቢኤስ የዩቱብ ቻነል ” ድጋፍ ማድረጊያ መርሀ ግብር ስለሚጀመር…
“ ለአእምሮ ህሙማን ብቻ በየወሩ እስከ 5 ሚሊዮን ብር መድኃኒት እንገዛለን። የህክምና ባለሙዎች እጥረት አለብን ” - የመቄዶኒያ ህክምና ክፍል

የመቄዶንያ አረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መረጃ ማዕከል ህክምና ክፍል የመድኃኒት መወደድና የስፔሻሊት ሀኪሞች እጥረት እንደፈተነው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

የማዕከሉ የህክምና ክፍል አስተባባሪ አቶ ዮናስ ሙሉጌታ በሰጡን ቃል፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ እውቀት ያለው በእውቀቱ፣ ጳጳሳቱ በጸሎታቸው እርዳታ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የማዕከሉ ህክምና ክፍል በዝርዝር ምን አለ?

በመቄዶንያ ካሉት 8,000 ሰዎች ወደ 2000 የሚሆኑት የአእምሮ ህሙማን ናቸው። የአእምሮ ህሙማኑ መድኃኒቶች ደግሞ ብዙ ጊዜ አገር ውስጥ አይገኙም።

ቢኖሩም ውስን ፋብሪካዎች ናቸው የሚያመርቷቸው ጥሬ እቃ ከውጪ አገር እያስመጡ። የተወሰኑ መድኃኒቶችም በቀጥታ ከውጪ አገር ነው የሚመጡት። 

ከገበያ የሚጠፉ መድኃኒቶችም አሉ ከምንዛሪ እጥረት ጋር በተያያዘ። መድኃኒቶቹ መጥፋታቸው ህሙማኑ ህመሙ እንዲያርሽባቸው ይዳርጋቸዋል። ወደ ጤንነታቸው ለመመለስም ጊዜ ይወዳል።

አዲስ አበባ፣ ሰንዳፋ፣ ፃድቃኔ፣ ሶማሌ ክልል ጎዴ፣ አማራ ክልል ደሴ፣ ሀረር፣ ድሴዳዋ በብዛት የአእምሮ ህሙማን የሚገኙባቸው ቦታዎች ናቸው። 

በመቄዶንያ ደግሞ የአእምሮ ህሙማንና አረጋዊያን ብቻ ሳይሆኑ ያሉት የደም ግፊት፣ ስኳር፣ አስም፣ ካንሰር፣ የኩላሊት (ዲያሌሲስ የሚያደርጉ) ህሙማንም አሉ። 

የአእምሮ ህሙማን መድኃኒቶች በጣም ውድ ናቸው። የምንገዛው ከኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ነው። ለአእምሮ ህሙማን ብቻ በየወሩ እስከ 5 ሚሊዮን ብር እንገዛለን። የህክምና ባለሙያዎች እጥረት አለብን”
ብሏል።

“ካለው ቁጥር አንጻር የባለሙያዎች ቁጥር በቂ አይደለም። ሳይካትሪ እንኳ ወደ 18 ነው የሚሆኑት። ግን ስፔሻሊስቶች ያስፈልጉናል። ባለሙያዎች በበጎ ፈቃደኝነት እንዲያገለግሉ እንፈልጋለን” ሲልም ጥሪ አቅርቧል።

“በወር ለአንድ እንኳ ሰዓት የህክምና አገልግሎት ቢሰጡ ለህሙማኑ ቀላል አይደለም” ያሉት የህክምና ክፍሉ፣ “የአእምሮ ስፔሻሊቲ፣ የዓይን፣ የጥርስ፣ የፊዚዮትራፒ፣ የሳይኮሎጁ ባለሙያዎች እጥረት አለብን” ብለዋል።

በሙያቸው ወደ ውጪ አገር ሂደው በትላልቅ የህክምና ተቋማት፣ ፋብሪካዎች የሚሰሩ ወገኖች መድኃኒት ቢልኩላቸው መቄዶንያ በህጋዊ መንገድ ፕሮሰስ አድርጎ መቀበል እንደሚችል፣ ድጋፉ ቢገኝ ህሙማን ሳያቋርጡ ህክምናቸውን መከታተል እንደሚችሉ ተመልክቷል።

#ማስታወሻ : የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በSiefu Show Tube ላይ ድጋፍ ለማድረግ ይዘጋጁ።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
886🙏157👏31😭25🕊21🥰15🤔8😱2