TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ፍትሕ

በሀገራችን በተደጋጋሚ ጊዜ ሴቶች ፣ ትንንሽ ህጻናት ሳይቀሩ ይደፈራሉ ፤ ይገደላሉ የሚሰጠው ፍርድ ግን " እውነት ፍርዱ ለማስተማር ነው ? ፍትሕ ለማስፈን ነው ? " የሚል ጥያቄ የሚያስነሳና እጅግ በጣም አስደንጋጭ ጭምር ነው።

ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦቻችን ፥ መቼም ስለ ሚደፈሩ ሴቶች ፤ ደጉን ከክፉ ያለዩ ምንም የማያውቁ ህጻናት ሳይቀሩ ስለሚፈጸምባቸው አሰቃቂ ግፍና ወንጀለኞች ላይ ስለሚተላለፉት ፍርዶች ብዙ ጊዜ መረጃ ስንለዋወጥ መቆየታችን ይታወሳል።

ለአብነት በቅርብ ወራት እንኳን ፦

- " የ11 ዓመቷን ልጅ የደፈረው አባት 16 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት ተቀጣ። "

- " አንገቷን አንቆና አፏ ውስጥ ጨርቅ ጠቅጥቆ የ14 ዓመቷን ልጅ የደፈረው እና ሕይወቷ እንዲያልፍ ያደረገው ግለሰብ በ19 ዓመት ተቀጣ። "

- " የ5 ዓመቷን ህፃን የደፈረው የ17 ዓመት ወጣት በ6 ወር እስር ተቀጣ። "

- " የ10 አመቷን ህፃን ልጅ አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በ14 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ። "

- " የ4 አመቷን ህጻን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በ17 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ። "

- " የ8 አመት ህፃናትን አስገድዶ የደፈረው የ41 አመት ጎልማሳ በ10 አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ። "

- " እጅግ አረመኔያዊ በሆነ ሁኔታ ሁለት የ16 እና የ17 ዓመት ልጆቹን በአልኮል አደንዝዞ አስገድዶ የደፈረው አባት በ21 አመት ተቀጣ። "


የሚሉ እነዚህን መረጃዎች በቲክቫህ ገጻችሁ ላይ አንብባችኋል።

ይኸው ዛሬ ደግሞ ጆሮን ጭው ፤ ልብን ቀጥ የሚያደርግ የባህር ዳሯን የ7 ዓመት ህጻን ሔቨንን ጉዳይ ሰማን።

ህጻን ሔቨን ላይ እጅግ አሰቃቂ የመድፈር እና የግድያ ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ 25 ዓመት እንደተፈረደበት ተሰማ።

ጭራሽ ይህም እንዳይሆነ የግለሰቡ ቤተሰቦች፣ ጎረቤቶች ፣ አንዳንድ የፖሊስ አባላት ፣ ከፍትህ አካላት ጭምር ጥረት ሲያደርጉ ነበር።

በሔቨን ጉዳይ በርካቶች ልባቸው ተሰብሯል ፤ ተቆጥተዋል። የመንግስት አካላትም ስለ ጉዳዩ ፊት ለፊት ወጥተው ተናግረዋል።

እናት የፍትሕ እያለች ነው። ለፍትሕ እያነባች ነው።

የግለሰቡ ቤተሰቦችም #እህቱን ጨምሮ ስራ የምትሰራበት ቦታ ድረስ ተከታትለዋት መቀመጫ መቆሚያ አሳጥተዋት ስራ እንድትልቀ አድርገዋል።

ከፍርዱ በፊትም ብዙ ማስፈራሪያ ሲደረግባት ነበር። ኃላም እንደዛው።

ማስፈራሪያ እና ክትትሉ ብዙ ጊዜ ቤት እንድትለቅ አድርጓታል።

ዛሬም ለቅሶ ላይ ናት። እናት ዛሬም የፍትሕ ያላህ ትላለች።

" የት እንሂድ እንግዲህ ? ወይ ሌላ ሀገር የለን ? ለማን እንናገር ? ማንስ ይሰማናል ? የእውነት አምላክ እሱ ይፍረድ ነው " ቃሏ።

የሔቨን ጉዳይ የብዙዎች ነው።

የእናቷ አንባ የብዙዎች ነው።

ስንት እናቶች ናቸው ይሁኑ እውነተኛ ፍርድና ፍትሕ አጥተው ቤታቸውን ዘግተው እያለቀሱ ያሉት ?

መሰል ጉዳዮች ሰሞነኛ ጉዳይ እየሆኑ እያለፉ ነው።

አንድ ሰሞን ይወራል ከዛ ይተዋል። በቃ ሊባልና መፍትሄ ሊፈለግ ይገባል።

የወንጀለኞቹ መታሰር የልጆቻችንን  ህይወት እንኳ ባያስመልስም ትክክለኛ ፍርድ ግን ቢያንስ እንባ ያብሳል። ሌላውን ያስተምራል። አሁን እየሆነ ያለው ያ አይደለም።

ፍትሕ ይስፈን !
አስተማሪና ሀቀኛ ፍርድ ይፈረድ !
ፍትሕ ! እውነተኛ ፍትሕ ለተነፈጉ በርካታ ሴቶች፣ እናቶች ፣ ህጻናት !

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
😭9K🙏592489😡294😢119👏103🕊97😱40🤔25🥰21
#ፍትሕ

" አያንቱ ላይ የግብረ-ስጋ ድፍረት ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በፖሊስ አዛዥ ተባባሪነት እንዲሸሽ ተደርጓል " - የአያንቱ ታላቅ ወንድም

🚨 " ፖሊስ አዛዡን ከኃላፊነት ከማዉረድ የዘለለ ደፋሪዉን ለሕግ አቅርቦ ዉሳኔ የማሰጠት ስራ አልተሰራም !! "

በሲዳማ ክልል፤ በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሻፋሞ ወረዳ ሹሮ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በእንጀራ አባቷ ቤት እያደገች የነበረች የ13 ዓመቷ ታዳጊ አያንቱ ቱና እሜ ለእናቷ መልዕክት ተልካ እየሄደች በነበረችበት ወቅት ባጥሶ በቀለ በተባለ ተጠርጣሪ ወጣት የግብረ-ስጋ ድፍረት ወንጀል ይፈጸምባታል።

በኋላም ተጠርጣሪዉ ተይዞ በሕግ ቁጥጥር ስር መዋል ሲገባዉ በፖሊስ አዛዥ ተባባሪነት በቤተሰቦቹ አማካኝነት ወደ ሌላ ክልል እንዲሸሽ መደረጉ ተነግሯል።

በወቅቱ የሻፋሞ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ የነበሩትና የወንጀል ድርጊቱን እንደፈጸመው ከተጠረጠረው ወጣት ጋር ባላቸዉ ዝምድና ምክንያት በጉዳዩ ላይ ቸልተኝነትን በማሳየት ተጠርጣሪው ከአከባቢው እንዲሸሽ ስለማስደረጋቸው የአያንቱ ታላቅ ወንድም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ከፍተኛ አካላዊና ስነልቦናዊ ጉዳት የደረሰባት ታዳጊዋ አያንቱ በቦና አጠቃላይ ሆስፒታል ስትታከም ቆይታ በአሁኑ ወቅት ወደ ሀዋሳ ተወስዳ በጣሊታ የሕፃናት ማቆያ እንደምትገኝ የሚናገረው ወንድሟ " ፖሊስ አዛዡን ከኃላፊነት ከማዉረድ የዘለለ ደፋሪዉን ለሕግ አቅርቦ ዉሳኔ የማሰጠት ስራ አልተሰራም " ብሏል።

" አያንቱ በአካልና በስነልቦና በእጅጉ ተጎድታ ከትምህርት ገበታዋም ተለይታ ፍትሕ ሳይሰጣት በጣሊታ የሕፃናት ማቆያ ከ1 ዓመት በላይ እንድትቀመጥ መደረጉ እጅግ በጣም ጎድቷታል " ሲል ገልጿል።

" የክልሉ ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ' ጉዳዩን ለምን በሚዲያ አወጣህ ሚዲያ ፍትህ ያሰጥህ ' ብለዉኛል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ይፋረደኝ እንጂ እኔ ገና የዩኒቨርሲቲ ተማሪና አባታችን በሕይወት የሌለ፤ እናታችንም ሌላ ሰዉ አግብታ የምትኖር ምስኪኖች ነን " ሲል ታላቅ ወንድሟ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

የፍትህ አካላት ምን አሉ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳይ ላይ የፍትህ አካላትን ምላሽ ለማካተት ፦
° የማዕላዊ ሲዳማ ዞን ዐቃቤ ሕግ መምሪያ
° የወረዳዉ ፍትህ ጽ/ቤት
° የወረዳና የዞኑን ፖሊስ
° የሻፋሞ ወረዳ ሴቶችና ሕፃናት ወጣቶች ጉዳይ መምሪያና የክልሉን ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮን ለማነጋገር ሞክሯል።

የሻፋሞ ወረዳ ፖሊስ ምን አለ ?

የሻፋሞ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ሙሴ አወል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት በወቅቱ የነበሩት የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ከኃላፊነት መነሳታቸዉን አስታወሰዋል።

እሳቸዉ ወደ አዛዣነት ከመጡ በኋላ ተጠርጣሪዉን የማፈላለጉ ስራ በተለያዩ ቴክኒኮች እየተሰራ ስለመሆኑ ገልፀዋል።

እስካሁን የተደረጉ ጥረቶች ለምን ዉጤታማ አልሆኑም ? በሚል ትክቫህ ኢትዮጵያ ላነሳላቸዉ ጥያቄ " ፖሊስ የሚችለዉን ሁሉ እያደረገ ነው " ሲሉ መልሰዋል።

የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ፍትሕ መምሪያ ምን አለ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸዉ የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ዐቃቤ ህግ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደማምሰዉ ታፈሰ ፥ ዐቃቤ ህግ ጉዳዩን በቀረበለት መረጃና ማስረጃ ልክ ተመልክቶ ክስ በማዘጋጀት ሂደት ላይ እያለ ተጠርጣሪዉ እንዲሸሽ መደረጉንና የቀድሞ የሻፋሞ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ከኃላፊነት እንዲነሱ መደረጉን ተናግረዋል።

አሁንም ቢሆን ተጠርጣሪውን አፈላልጎ ለህግ በማቅረቡ ሂደት ፖሊስ እያደረገ ያለዉን ክትትል በማጣራት በህግ አግባብ መሰረት ቀጣይ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታዉቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የሲዳማ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የሴቶች ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ፍፁም በላይነህን ለማግኘት መክሯል።

ኃላፊዋ በስልክ መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።

ይህም በመሆኑ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሁለት ጊዜ በአካል ቢሯቸው ተገኝቶ ኃላፊዋን ለማነጋገር ቢሞክርም ፈቃደኛ ባለመሆናቸዉ ሃሳባቸው ሳይካተት ቀርቷል።

ጉዳዩን እስከመጨረሻው ድረስ የምንከታተለው ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
2😡1.97K😭384239🙏178💔104😢31🥰21😱21👏19🕊17🤔12