TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " ጊዚያዊ አስተዳደር ተቆጥረው የተሰጡት ስራዎች አሉት ፤ ስራዎቹን ፍፅሞ ስልጣኑ ያስረክባል " - አቶ ጌታቸው ረዳ ትናት የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ፤ ከነሀሴ 9 አስከ 11/2016 ዓ.ም  " ትግራይ ከአስከፊውና ደም አፋሳሽ  ጦርነት ወደ ከፍታ ወይስ ወደ ብዥታ ጉዞ !! " በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የትግራይ ሙሁራን ማህበር ያዘጋጀው የውይይት መድረክ…
#አሁን : በመቐለ ከተማ በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ በወቅታዊ የህወሓት የፓለቲካ ሁኔት ላይ ያተኮረ ውይይት እየተካሄደ ነው።

በውይይቱ መድረኩ ላይ " 14ኛው የህወሓት ጉባኤ ህጋዊ አይደለም " ብለው የተቃወሙ ፦
➡️ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ፣
➡️ የድርጅቱ የማእከላዊ ቁጥጥር ኮሚሽን ፣
➡️ የክልል ፣ የዞን ፣ የወረዳና ሌሎች አመራሮች በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።

የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ፥ " የውይይት መድረኩ ህወሓትን ለማዳንና ትግራይን ወደ ነባራዊ ሁኔታዋ ለመመለስ ወሳኝ ነው " ማለታቸውን ከድምጺ ወያነ ቴሌቪዥን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

ተጨማሪ ይኖረናል።

የፎቶ ባለቤት ፦ ድምጺ ወያነ

@tikvahethiopia
1.04K🕊217😡118🤔117😭71🙏60👏54🥰48😱37😢30
#አሁን : የቀድሞ የትግራይ ተዋጊዎችን ትጥቅ ማስወረድና ወደ ተሃድሶ ማዕከላት የማስገባት ስራ ዛሬ ተጀመረ።

የመጀመሪያው ዙር የትግራይ የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞብላይዝድ በማድረግ ወደ ስልጠና ማእከላት የማስገባት ስራ በመቐለ ከተማ በይፋ ተጀምሯል።

በመጀመሪያ ዙር በክልሉ 75 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎች ስልጠናና የማቋቋምያ ገንዘብ በመስጠት ወደ ህብረተሰቡ የማቀላቀል ስራ ይሰራል።

በአሁን ሰዓት ታጣቂዎች የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ፣ የትግራይ ክልል የፀጥታ ሃይሎች ከፍተኛ አመራሮች ፣ የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪዎች እና ሚድያዎች ፊት የታጠቁትን ቀላል መሳሪያ እያስረከቡ ነው።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል በስፍራው ተገኝቶ ሁነቱን እየተከታተለ ነው።

ዝርዝር እናቀርባለን !

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
485🕊223🤔109😡64👏54🙏33😢18😱12🥰9
#አሁን

ኢትዮ ቴሌኮም በዛሬው ዕለት " ዘመን ገበያ " የተሰኘ የዲጂታል ግብይት ፕላትፎርም (Digital Market Place Platform) አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐግብር በሳይንስ ሙዚየም እያካሄደ ይገኛል።

ተጨማሪ መረጃዎች ተከታትለን የምናደርሳችሁ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia
283😡133👏34🙏30😭18🤔15😢10🕊8🥰6💔6😱1