TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Bahirdar

በአማራ ክልል መዲና ባሕርዳር ከተማ ተጥለው ከነበሩ ክልከላዎች ከፊሎቹ መነሳታቸውን የከተማው የጸጥታ ም/ቤት ዛሬ ምሽት አሳወቀ።

ምክር ቤቱ ፤ ማንኛውም የንግድ እንቅስቃሴ ያለገደብ 24 ሰዓት ክፍት በማድረግ እንዲሰሩ ወስኗል።

ከባጃጅ እና ከሞተር ሳይክል ውጭ ሁሉም ተሽከርካሪዎች ያለገደብ እንዲንቀሳቀሱም ውሳኔ አሳልፏል።

በተጨማሪ ማንኛውም ሰው ያለምንም የሰዓት ገደብ እንዲንቀሳቀስ የጸጥታ ም/ቤቱ ወስኗና።

ምክር ቤቱ ማሻሻያ ያልተደረገባቸውና አሁንም የተጣሉ ግዴታዎች እንዳሉ አስገንዝቧል።

➡️ ማንኛውም ተሽከርካሪ በሚንቀሳቀስበት ጊዜ የፊት ለፊትና የኋላ ሰሌዳ አሟልቶ መንቀሳቀስ እንዳለበት ይህንን ሳያደርግ ተገኝቶ በጸጥታ ሀይሉ ለሚወሰደው ማንኛውም ህጋዊ እርምጃ ሀላፊነቱን ራሱ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።

➡️ ማንኛውም እግረኛ ሲንቀሳቀስ ማንነቱን የሚገልጽ የቀበሌ የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት አለበት ብሏል።

➡️ የጸጥታ ሀይሉና በሚኖሩበት ቀበሌ ወይም ቀጠና ወይም ብሎክ ብቻ መሳሪያ ይዘው እንዲንቀሳቀሱ ከፈቀደላቸው መሳሪያ ፈቃድ ኩፖን ከተሰጣቸው ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም የተከለከለ መሆኑ አስገንዝቧል።

➡️ የባጃጅ ተሽከርካሪ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት በኋላ ይዞ መንቀሳቀስ ክልክል መሆኑን አሳውቋል።

➡️ ባለ 2 እግር ሞተር በማንኛውም ሁኔታ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም የተከለከለ እንደሆነ አስጠንቅቋል።

#BahirdarCity

@tikvahethiopia
661🙏59🕊43😡41🤔21😭10👏9😢9🥰1