TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ትምህርት ቤቶች ባቀረቡት የዋጋ ጭማሪ ፕሮፖዛል ላይከወላጆች ጋር መግባባት ላይ መድረስ ካልተቻለ ባለሥልጣኑ ውሳኔ የሚሰጥ ይሆናል " - የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኙ 1,227 የግል ትምህርት ቤቶች በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን እስከ 65 በመቶ ድረስ የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪ እንዲያደርጉ እንደተፈቀደለቸው መዘገቡ ይታወሳል። ጭማሪውን ተከትሎ የአዲስ…
#AddisAbaba

የትምህርት ቤት ክፍያ !

20 በመቶ ትምህርት ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር አለመስማማታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በቅርቡ ባጸደቀው የግል ትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሰራር ስርአት ደንብ ቁጥር 194/2017 መሰረት በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ላይ ከ ተማሪ ወላጅና አሳዳጊዎች ጋር ካልተስማሙ መንግስታዊ ካልሆኑ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት መካሄዱን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በውይይት መርሃ ግብሩ ፦
- የትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ፣
- የትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ከፍተኛ አመራሮች
- የግል ትምህርት ቤቶች አሰሪዎች ማህበር ፣
- የግል ትምህርት ቤት ባለቤቶች እና የተማሪ ወላጅ ኮሚቴ ተወካዮች እንደ ተሳተፉ ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል።

ውይይቱ የተካሄደው በጭማሪው ላይ መስማማት ላይ ያልደረሱ ትምህርት ቤቶች ደንቡ በሚያስቀምጠው መሰረት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ውሳኔ ያሳለፈ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ አስተሳሰብ ለመያዝ እንዲቻል መሆኑን ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ "በደንቡ መሰረት 80 ፐርሰንት ያህል ትምህርት ቤቶች ከወላጆችና አሳዳጊዎች ጋር በመስማማት የአገልግሎት ክፍያ መጨመራቸው የሚበረታታ ተግባር ነው" ብለዋል።

እንደ ትምህርት ቢሮ ሃላፊው ገለጻ 20 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ከክፍያ ጭማሪ ጋር በተያያዘ ከወላጆች እና አሳዳጊዎች መስማማት ላይ አለመድረሳቸውን አመላክቷል።

የትምህርትና ስልጠናና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢዘዲን ሙስባህ "በደንቡ ላይ በመግባባት ወደ ስራ መገባቱን በዚህም መሰረት በርካታ ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር በመስማማት መጨመራቸውን ፣ መመሪያውን መሰረት በማድረግም ባለስልጣኑ በተቀሩትና መስማማት ባልቻሉት ላይ  ውሳኔ መስጠቱን" አሳውቀዋል ።

ባለሥልጣኑ ምን ውሳኔ እንዳሳለፈ በዝርዝር ባይገለጽም የወላጆችን የመክፈል አቅም እና የትምህርት ተቋማቱን የግብአት አቅርቦት ታሳቢ አድርጎ ተግባራዊ የሆነ መሆኑን ስለመናገራቸው ትምህርት ቢሮው አሳውቋል።

#AddisAbabaEducationBureau

@tikvahethiopia
404😭57😡40🕊10🤔8😢8😱4