#Arbaminch
በአርባ ምንጭ ከተማ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚሰሩ ህጻዎች ከፍታቸው G+6 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን ስታንዳርድ ተቀመጠ።
የከተማ ህንፃ ቀለማት ምርጫም ነጭና ቢጫ ውህድ ፤ አንድ ህንፃ መቀባት ያለበትም ሶስት አይነት ቀለም ብቻ ነው ተብሏል።
" በኮሪደር የሚለሙ ቋሚ አጥር ግንባታ 1.50 ሜትር ፤ በሚካሄዱ ግንባታዎች ጊዜያዊ አጥሮች ከሁለት ሜትር በላይ ከፍታ ያላቸው ሆነው አረንጓዴ ቀለም በኤጋ ቆርቆሮ ማጠር " እንደሚገባ ተገልጿል።
ዝቅተኛ ህንፃዎች ከመንገድ መራቅ ያለባቸው ርቀት (set back) አደባባዮች ዙሪያ 6 ሜትር፣ ለሌች መንገዶችን ተከትሎ 4 ሜትር፣ ከግለሰቦች ወሰን በኩል መሰኮት ከሌለው 2 ሜትር፣ መስኮት ካለው 3 ሜትር ርቀት መኖር አለበት ተብሏክ።
ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በቀንና በማታ ዕይታን የማይረብሽ ውብና ሳቢ መንገድ ዳር መብራት ቀለም የመብራት ቀለም ከ3000K Warm LED በከተማው በሁሉም ዋና መስመሮች በከተማ ውስጥ ያሉ ንግድና ግለሰብ ቤቶች፣ ድርጅቶችና መንግስታዊ እና ሌሎች ተቋማት የማውጣት ግዴታ እንዳለባቸው ስታንዳርድ ተቀምጧል።
አዲስ አበባ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ ወደ ክልሎችም የሄደ ሲሆን የኮሪደር ስራ እየተሰራባቸው ካሉ ከተሞች አንዷ አርባ ምንጭ ናት።
@tikvahethiopia
በአርባ ምንጭ ከተማ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚሰሩ ህጻዎች ከፍታቸው G+6 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን ስታንዳርድ ተቀመጠ።
የከተማ ህንፃ ቀለማት ምርጫም ነጭና ቢጫ ውህድ ፤ አንድ ህንፃ መቀባት ያለበትም ሶስት አይነት ቀለም ብቻ ነው ተብሏል።
" በኮሪደር የሚለሙ ቋሚ አጥር ግንባታ 1.50 ሜትር ፤ በሚካሄዱ ግንባታዎች ጊዜያዊ አጥሮች ከሁለት ሜትር በላይ ከፍታ ያላቸው ሆነው አረንጓዴ ቀለም በኤጋ ቆርቆሮ ማጠር " እንደሚገባ ተገልጿል።
ዝቅተኛ ህንፃዎች ከመንገድ መራቅ ያለባቸው ርቀት (set back) አደባባዮች ዙሪያ 6 ሜትር፣ ለሌች መንገዶችን ተከትሎ 4 ሜትር፣ ከግለሰቦች ወሰን በኩል መሰኮት ከሌለው 2 ሜትር፣ መስኮት ካለው 3 ሜትር ርቀት መኖር አለበት ተብሏክ።
ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በቀንና በማታ ዕይታን የማይረብሽ ውብና ሳቢ መንገድ ዳር መብራት ቀለም የመብራት ቀለም ከ3000K Warm LED በከተማው በሁሉም ዋና መስመሮች በከተማ ውስጥ ያሉ ንግድና ግለሰብ ቤቶች፣ ድርጅቶችና መንግስታዊ እና ሌሎች ተቋማት የማውጣት ግዴታ እንዳለባቸው ስታንዳርድ ተቀምጧል።
አዲስ አበባ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ ወደ ክልሎችም የሄደ ሲሆን የኮሪደር ስራ እየተሰራባቸው ካሉ ከተሞች አንዷ አርባ ምንጭ ናት።
@tikvahethiopia
👏545😡189❤117😢75🤔41😭23🙏21😱18🥰15🕊11
#ArbaMinch : ላለፉት በርካታ ዓመታት አርባ ምንጭ ላይ ሲገነባ የቆየው የጋሞ አደባባይ ተመርቋል።
" አደባባዩ በዞኑ የሚገኙ ህዝቦችን ባህል እና ትዉፊት በሚወክል መልኩ ነው የተሰራው " ሲል የዞኑ አስተዳደር ገልጿል።
ለዚህ አደባባይ ከ122,000,000 ብር (መቶ ሃያ ሁለት ሚሊዮን ብር) በላይ ወጪ እንደተደረገበት ነው የተነገረው።
@tikvahethiopia
" አደባባዩ በዞኑ የሚገኙ ህዝቦችን ባህል እና ትዉፊት በሚወክል መልኩ ነው የተሰራው " ሲል የዞኑ አስተዳደር ገልጿል።
ለዚህ አደባባይ ከ122,000,000 ብር (መቶ ሃያ ሁለት ሚሊዮን ብር) በላይ ወጪ እንደተደረገበት ነው የተነገረው።
@tikvahethiopia
😱1.61K😡841❤387😭257👏153🤔152🕊79🙏50🥰42😢37
#ArbaMinch
🔴 የእሳት አደጋ መድረሱን ተከትሎ የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ የነበሩ እናት ህይወት አለፈ።
በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ረፋድ 4 ሠዓት አከባቢ በተለምዶ ' ቡቡ ሜዳ ' ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በሚገኘዉ አዲሱ ገበያ የእሳት አደጋ ተከስቶ በንብረት ላይ ዉድመት ማድረሱን የከተማው አስተዳደር ፖሊስ አስታውቋል።
በእሳት አደጋዉም የሰዉ ሕይወት መጥፋቱን የሚገልፁ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስን ማብራሪያ ጠይቋል።
የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ፤ በአከባቢው በሚገኝ አንድ የኤሌክትሮንክስ ሱቅ ዉስጥ በኤሌክትሪክ ኮንታክት ምክንያት በተነሳ የእሳት አደጋ 12 ሱቆች መዉደማቸዉን ገልጸዋል።
በአደጋው ወቅት በገበያው ዉስጥ በተለምዶ መንገድ በጩኸት ይድረሱልን ጥሪ ሲያደርጉ ከነበሩ ሴቶች መካከል አንዲት እናት ባለባቸው የጤና እክል ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
እኚህ እናት የልብ ሕመም እንደነበራቸው የገለጹት ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ፤ በጩኸት የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ ሳለ በመድከማቸው ወደ ነጭ ሳር ሆስፒታል ቢወሰዱም ሕይወታቸው ማርተፍ አልተቻለም ነው ያሉት።
ሆኖም በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሕይወቷ ያለፈዉ በእሳት አደጋዉ በደረሰ ጉዳት ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ የተሳሳተ ነዉ ብለዋል።
በገበያዉ ዉስጥ ያለዉ የሱቆች አሰራር እና አጠቃቀም ለእሳት አደጋ አጋላጭ ነዉ ያሉት አዛዡ ፤ ሕይወቷ ያለፈዉ ግለሰብ በገበያው ዉስጥ ሱቅ እንደነበራቸውና ሱቃቸዉም እሳት አደጋዉ እንዳልደረሰበት ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የእሳት አደጋዉ በተገለፀው አኳሃን መፈጠሩን በገበያው ውስጥ ካሉ ነጋዴዎች የሰማ ሲሆን ሕይወታቸዉ ያለፈዉ ግለሰብም በቀጥታ በእሳት አደጋው በደረሰ ጉዳት አለመሆኑን ነጋዴዎች ተናግረዋል።
" ሞች ወ/ሮ አበባየሁ መንገሻ እንደ እናት ያሳደጉኝ እናቴ ናቸዉ፤ የሞቱት በእሳት አደጋዉ አይደለም " ያሉት አቶ አማኑኤል ሰይፉ የተባሉ ነጋዴ አስቀድመው የልብ ሕመምና የሕክምና ክትትል እንደነበራቸው አስረድተዋል።
አክለው በእሳት አደጋዉ ወቅት መደንገጣቸዉና ከሌሎችም ሴቶች ጋር ሆነዉ ለይድረሱልን ብዙ መጮኻቸዉን ተከትሎ መዳከማቸዉንና ወደ ነጭ ሳር ሆስፒታል ቢወሰዱም ሕይወታቸው ማለፉን ነው የገለጹት።
#TikvahEthiopiaFamilyArbaMinch
@tikvahethiopia
🔴 የእሳት አደጋ መድረሱን ተከትሎ የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ የነበሩ እናት ህይወት አለፈ።
በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ረፋድ 4 ሠዓት አከባቢ በተለምዶ ' ቡቡ ሜዳ ' ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በሚገኘዉ አዲሱ ገበያ የእሳት አደጋ ተከስቶ በንብረት ላይ ዉድመት ማድረሱን የከተማው አስተዳደር ፖሊስ አስታውቋል።
በእሳት አደጋዉም የሰዉ ሕይወት መጥፋቱን የሚገልፁ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስን ማብራሪያ ጠይቋል።
የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ፤ በአከባቢው በሚገኝ አንድ የኤሌክትሮንክስ ሱቅ ዉስጥ በኤሌክትሪክ ኮንታክት ምክንያት በተነሳ የእሳት አደጋ 12 ሱቆች መዉደማቸዉን ገልጸዋል።
በአደጋው ወቅት በገበያው ዉስጥ በተለምዶ መንገድ በጩኸት ይድረሱልን ጥሪ ሲያደርጉ ከነበሩ ሴቶች መካከል አንዲት እናት ባለባቸው የጤና እክል ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
እኚህ እናት የልብ ሕመም እንደነበራቸው የገለጹት ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ፤ በጩኸት የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ ሳለ በመድከማቸው ወደ ነጭ ሳር ሆስፒታል ቢወሰዱም ሕይወታቸው ማርተፍ አልተቻለም ነው ያሉት።
ሆኖም በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሕይወቷ ያለፈዉ በእሳት አደጋዉ በደረሰ ጉዳት ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ የተሳሳተ ነዉ ብለዋል።
በገበያዉ ዉስጥ ያለዉ የሱቆች አሰራር እና አጠቃቀም ለእሳት አደጋ አጋላጭ ነዉ ያሉት አዛዡ ፤ ሕይወቷ ያለፈዉ ግለሰብ በገበያው ዉስጥ ሱቅ እንደነበራቸውና ሱቃቸዉም እሳት አደጋዉ እንዳልደረሰበት ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የእሳት አደጋዉ በተገለፀው አኳሃን መፈጠሩን በገበያው ውስጥ ካሉ ነጋዴዎች የሰማ ሲሆን ሕይወታቸዉ ያለፈዉ ግለሰብም በቀጥታ በእሳት አደጋው በደረሰ ጉዳት አለመሆኑን ነጋዴዎች ተናግረዋል።
" ሞች ወ/ሮ አበባየሁ መንገሻ እንደ እናት ያሳደጉኝ እናቴ ናቸዉ፤ የሞቱት በእሳት አደጋዉ አይደለም " ያሉት አቶ አማኑኤል ሰይፉ የተባሉ ነጋዴ አስቀድመው የልብ ሕመምና የሕክምና ክትትል እንደነበራቸው አስረድተዋል።
አክለው በእሳት አደጋዉ ወቅት መደንገጣቸዉና ከሌሎችም ሴቶች ጋር ሆነዉ ለይድረሱልን ብዙ መጮኻቸዉን ተከትሎ መዳከማቸዉንና ወደ ነጭ ሳር ሆስፒታል ቢወሰዱም ሕይወታቸው ማለፉን ነው የገለጹት።
#TikvahEthiopiaFamilyArbaMinch
@tikvahethiopia
😭1.59K😢199❤149🕊64😡31🙏21😱19🥰17👏16🤔15