TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኬንያ

ባለፈው ሳምንት በኬንያ፣ ናይሮቢ አንድ ፖሊስ ጣቢያ አቅራቢያ በሚገኝ የቆሻሻ መጣያ ስፍራ የተቆራረጠ የሴቶች አካል በማዳበሪያ ተጥሎ ተገኝቷል።

የተቆራረጠው የሴቶች አካል ከተገኘ በኋላም ከ40 በላይ ሴቶችን መግደሉን ያመነ ግለሰብ መያዙን የኬንያ ፖሊስ ዛሬ አስታውቋል።

ባለቤቱን ጨምሮ 42 ሴቶችን መግደሉን ያመነው የ33 ዓመት ተጠርጣሪ የተያዘው በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ቢያንስ የ8 ሴቶች አስከሬን ከተገኘ በኋላ ነው።

ኮሊንስ ካሃሊሲአ የተባለው ይኸው ተጠርጣሪ እኤአ 2022 ጀምሮ ሴቶችን ብቻ እየለየ ሲገድል እንደቆየ ቃሉን መስጠቱን የኬንያ ፖሊስ አስታውቋል።

ተጠርጣሪው በሰጠው ቃል " ውብ የሆኑ ሴቶችን " መግደል እንደሚመርጥ ጨምሮ ተናግሯል።

የወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት " ለሰው ልጅ ሕይወት ምንም ደንታ የሌለው ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር አውለናል " ብሏል።

ፖሊስ እንደሚለው ከሆነ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ያዋለው ከገደላቸው ሴቶች ከአንዷ ሞባይል ወደራሱ ስልክ ገንዘብ ከላከ በኋላ ነው።

ተጠርጣሪው ኮሊንስ የሚኖረው የሴቶቹን አስክሬን ሲጥል ከነበረበት የቆሻሻ መጣያ ስፍራ 500 ሜትር ርቀት ላይ ነው።

የዚህ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋል የተሰማው ባለፉት ቀናት ከቆሻሻ መጣያው ስፍራ የበርካታ ሴቶች የተቆራረጡ አካላት በማዳበሪያ ተጥሎ ከተገኘ በኋላ ነው።

የተገደሉት ሴቶች እድሜያቸው ከ18 እስከ 30 ሲሆን ሁሉም በተመሳሳይ መንገድ ነው የተገደሉት።

ግለሰቡ ወንጀሉን ለምን እንደፈጸመ ፖሊስ እያጣራ ሲሆን የአስክሬን ምርመራም እየተደረገ ይገኛል።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
😱767😭520111😡87😢53🕊19👏18🤔15🙏14🥰9