" የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት መዘዙ ለአጎራባች ሃገራትም ተርፏል " - ካተሪን ፓቲሎ
የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት በሱዳን ላይ ካስተለው ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት ባሻገር ኢትዮጵያን ጨምሮ በአጎራባች ሃገራት ላይ ብርቱ ኤኮኖሚያዊ ጉዳት ማድረሱን የዓለም የገንዘብ ድርጅት አስታወቀ።
በድርጅቱ የአፍሪቃ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ካተሪን ፓቲሎ " የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት መዘዙ ለአጎራባች ሃገራትም ተርፏል " ብለዋል።
" ቀድሞውኑ በራሳቸው የውስጥ ጉዳዮቻቸው ተይዘው የነበሩ የሱዳን ተጎራባቾች በስደተኞች መጥለቅለቅን ጨምሮ ሌሎች የደህንነት እና የንግድ ተግዳሮቶች አስከትሎባቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
የዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም የትንበያ ሪፖርት እንደሚያመለክተው በጦርነቱ በተለይ በማዕከላዊ አፍሪቃ ፣ ቻድ ፣ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን ላይ ከፍተኛ ኤኮኖሚያዊ ጉዳት ሊደርስ ይችላል።
በተለይ ከገቢዋ አብዛኛውን ከነዳጅ ዘይት ሽያጭ የምታገኘው ደቡብ ሱዳን ባለፈው የካቲት ወር ሱዳን ውስጥ ከዋነኞቹ የነዳጅ ዘይት ማስተላለፊያዎች ቱቦዎች በአንዱ ላይ ጉዳት ከደረሰባት በኋላ ነገሮች አሳሳቢ መሆናቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
በተመሳሳይ በመካከለኛው ምስራቅ እና በዩክሬን እየተካሄዱ ያሉ ሌሎች " ውጫዊ ግጭቶች " እንደ የምግብ ዋጋ ፣ ማዳበሪያ እና የኃይል ወጪዎች ላይ ተጽዕኖ ማሳደራቸውን የዓለም የገንዘብ ድርጅት ገልጿል። #ዶቼቨለሬድዮ
@tikvahethiopia
የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት በሱዳን ላይ ካስተለው ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት ባሻገር ኢትዮጵያን ጨምሮ በአጎራባች ሃገራት ላይ ብርቱ ኤኮኖሚያዊ ጉዳት ማድረሱን የዓለም የገንዘብ ድርጅት አስታወቀ።
በድርጅቱ የአፍሪቃ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ካተሪን ፓቲሎ " የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት መዘዙ ለአጎራባች ሃገራትም ተርፏል " ብለዋል።
" ቀድሞውኑ በራሳቸው የውስጥ ጉዳዮቻቸው ተይዘው የነበሩ የሱዳን ተጎራባቾች በስደተኞች መጥለቅለቅን ጨምሮ ሌሎች የደህንነት እና የንግድ ተግዳሮቶች አስከትሎባቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
የዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም የትንበያ ሪፖርት እንደሚያመለክተው በጦርነቱ በተለይ በማዕከላዊ አፍሪቃ ፣ ቻድ ፣ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን ላይ ከፍተኛ ኤኮኖሚያዊ ጉዳት ሊደርስ ይችላል።
በተለይ ከገቢዋ አብዛኛውን ከነዳጅ ዘይት ሽያጭ የምታገኘው ደቡብ ሱዳን ባለፈው የካቲት ወር ሱዳን ውስጥ ከዋነኞቹ የነዳጅ ዘይት ማስተላለፊያዎች ቱቦዎች በአንዱ ላይ ጉዳት ከደረሰባት በኋላ ነገሮች አሳሳቢ መሆናቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
በተመሳሳይ በመካከለኛው ምስራቅ እና በዩክሬን እየተካሄዱ ያሉ ሌሎች " ውጫዊ ግጭቶች " እንደ የምግብ ዋጋ ፣ ማዳበሪያ እና የኃይል ወጪዎች ላይ ተጽዕኖ ማሳደራቸውን የዓለም የገንዘብ ድርጅት ገልጿል። #ዶቼቨለሬድዮ
@tikvahethiopia
🕊186❤85😭51🙏21😢19😱11🥰9😡8👏7