TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz ° “ ኤሌክትሪክ ከተቋረጠ 3 ወር ሆነው። ጨለማ ውስጥ እየኖርን ነው” - የወምበራ ወረዳ ነዋሪዎች ° “ ከወረዳው መንግስት ጋር እየተየጋገርን ነው፤ በቅርቡ እንሰራዋለን ” - የደብረ ዘይት ማዕከል በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ ወምበራ ወረዳ ደብረ ዘይት ከተማ ኤሌክትሪክ በመቋረጡ ጨለማ ውስጥ ለመኖር መገደዳቸውን ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ። “ ኤሌክትሪክ ከተቋረጠ…
#BenishangulGumuz
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፤ አሶሳ ከተማ የኤሌክትሪክ ኃይል ከተቋረጠ 2 ሳምንት አልፏል።
የአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ አገልግሎት ሊቆም እንደሚችል አሳውቋል።
ሆስፒታሉ በየቀኑ ከ400 እስከ 500 ከዞን ፣ ከወረዳ፣ ከአጎራባቹ ኦሮሚያ ክልል ታካሚዎችን ያስተናግዳል።
ሆስፒታሉ ከሚሰጠው አገልግሎት አንጻር 24 ሰዓት ሙሉ የማይቋረጥ ኃይል ማግኘት ያለበር ቢሆንም ባለፉት ሳምንታት የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡ በተቋሙ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል።
ኃይል ከተቋረጠበት ቀን አንስቶ ለጄኔሬተር በየቀኑ ከ180 እስከ 200 ሊትር ነዳጅ እየተጠቀመ ነው።
ሁለት ጄኔሬተሮች ያሉ ቢሆንም ሙሉ ሆስፒታሉን ኃይል እንዲያገኝ የሚያስችሉ አይደሉም።
ያለ ጊዜያቸው የሚወለዱ ጨቅላ ሕጻናትን ለማቆየት የሚሆኑ ማሽኖችን ማስነሳትም ከባድ ሆኗል።
በዚህ ማሽን ውስጥ የሚቆዩ ሕጻናት ያልተቋረጠ ኦክስጅን ማግኘት ስላለባቸው ኃይል መቋረጥ ካጋጠመ በሕጻናቱ ላይ ሞት ሊያስከትል ይችላል።
ሆስፒታሉ የተወሰኑ የሥራ ክፍሎችን የኃይል አቅርቦት እያጠፋ ነው ጄኔሬተሩ ሲነሳ የኤሌክትሪክ ኃይሉን ወደ ጨቅላ ሕጻናት ማቆያ ማሽኑ የሚቀይረው። ሌሎች የሥራ ዘርፎች ላይ ኃይሉ ሲፈለግ ደግሞ ማሽኑን ለማቋረጥ ይገደዳል።
ቀድሞም የበጀት እጥረት የሚፈተነው ሆስፒታሉ ለጄኔሬተሩ የሚውለው ነዳጅ ወጪ ከአቅም በላይ እንደሆነ የነዳጅ ማከማቻም አለመኖር ፈተና እንደሆነ ገልጿል።
ሆስፒታሉ ነዳጅ ከተለያዩ መ/ቤቶች እና ባለሃብቶች በልመና ነው ማታ ማታ እየዞረ የሚያመጣው።
ሁኔታው በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ጭምር ሊቋረጥ የሚችልበት አዝማሚያ እንዳለ አሳውቋል።
የአሶሳ ዞን ፥ በአሶሳ ከተማ እና በአካባቢው የኃይል መቋረጥ የተከሰተው በአጎራባች የኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ወለጋ ዞን በሚገኝ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ላይ " በታጣቂዎች " በደረሰ ጉዳት እንደሆነ አሳውቋል።
#BBCAMHARIC
@tikvahethiopia
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፤ አሶሳ ከተማ የኤሌክትሪክ ኃይል ከተቋረጠ 2 ሳምንት አልፏል።
የአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ አገልግሎት ሊቆም እንደሚችል አሳውቋል።
ሆስፒታሉ በየቀኑ ከ400 እስከ 500 ከዞን ፣ ከወረዳ፣ ከአጎራባቹ ኦሮሚያ ክልል ታካሚዎችን ያስተናግዳል።
ሆስፒታሉ ከሚሰጠው አገልግሎት አንጻር 24 ሰዓት ሙሉ የማይቋረጥ ኃይል ማግኘት ያለበር ቢሆንም ባለፉት ሳምንታት የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡ በተቋሙ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል።
ኃይል ከተቋረጠበት ቀን አንስቶ ለጄኔሬተር በየቀኑ ከ180 እስከ 200 ሊትር ነዳጅ እየተጠቀመ ነው።
ሁለት ጄኔሬተሮች ያሉ ቢሆንም ሙሉ ሆስፒታሉን ኃይል እንዲያገኝ የሚያስችሉ አይደሉም።
ያለ ጊዜያቸው የሚወለዱ ጨቅላ ሕጻናትን ለማቆየት የሚሆኑ ማሽኖችን ማስነሳትም ከባድ ሆኗል።
በዚህ ማሽን ውስጥ የሚቆዩ ሕጻናት ያልተቋረጠ ኦክስጅን ማግኘት ስላለባቸው ኃይል መቋረጥ ካጋጠመ በሕጻናቱ ላይ ሞት ሊያስከትል ይችላል።
ሆስፒታሉ የተወሰኑ የሥራ ክፍሎችን የኃይል አቅርቦት እያጠፋ ነው ጄኔሬተሩ ሲነሳ የኤሌክትሪክ ኃይሉን ወደ ጨቅላ ሕጻናት ማቆያ ማሽኑ የሚቀይረው። ሌሎች የሥራ ዘርፎች ላይ ኃይሉ ሲፈለግ ደግሞ ማሽኑን ለማቋረጥ ይገደዳል።
ቀድሞም የበጀት እጥረት የሚፈተነው ሆስፒታሉ ለጄኔሬተሩ የሚውለው ነዳጅ ወጪ ከአቅም በላይ እንደሆነ የነዳጅ ማከማቻም አለመኖር ፈተና እንደሆነ ገልጿል።
ሆስፒታሉ ነዳጅ ከተለያዩ መ/ቤቶች እና ባለሃብቶች በልመና ነው ማታ ማታ እየዞረ የሚያመጣው።
ሁኔታው በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ጭምር ሊቋረጥ የሚችልበት አዝማሚያ እንዳለ አሳውቋል።
የአሶሳ ዞን ፥ በአሶሳ ከተማ እና በአካባቢው የኃይል መቋረጥ የተከሰተው በአጎራባች የኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ወለጋ ዞን በሚገኝ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ላይ " በታጣቂዎች " በደረሰ ጉዳት እንደሆነ አሳውቋል።
#BBCAMHARIC
@tikvahethiopia
😭507❤113😢53😱40😡32🙏26🤔21🕊21👏18🥰9
#USA #VISA
" የቪዛው የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር አጥሯል ፤ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትም ተከልክሏል " - ኤምባሲው
የአሜሪካ ኤምባሲ ለኢትዮጵያውያን የሚሰጠው ቪዛ የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ማጠሩን አስታውቋል።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስደተኛ ባልሆኑ የቪዛ አመልካቾች ላይ ባደረገው የፖሊሲ ለውጥ ምክንያት ውሳኔው መተላለፉን ኤምባሲው ገልጿል።
በአዲሱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፖሊሲ መሠረት፤ " ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለኢትዮጵውያን የሚሰጠው ቪዛ ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል እና የሦስት ወር ቆይታ " እንደሚኖረው አስታውቋል።
ኤምባሲው ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. በፊት የተሰጡ ቪዛዎች ባሉበት እንደሚቀጥሉ ገልጿል።
ለንግድ እና ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን የሚያገኙት ቪዛ "B1" እና "B2" በሚለው ምድብ ውስጥ ይካተታል።
እስካሁን በነበረው አሰራር በዚህ ምድብ ውስጥ የሚገቡ ተጓዦች የሚያገኙት ቪዛ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ነበር። በተጨማሪም የቪዛው የቆይታ ጊዜ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ያስችል ነበር።
አሁን ይፋ የተደረገው ፖሊሲ የቪዛውን የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ከማሳጠር በተጨማሪ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትን ከልክሏል።
በአዲሱ ፖሊሲ ቪዛ የሚያገኙ ተጓዦች የቆይታ ጊዜ ባይጠናቀቅም እንኳ ከአሜሪካ ከወጡ በኋላ በዚያው ቪዛ ተመልሰው መግባት አይችሉም።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለያዩ አፍሪካ አገራትን ቪዛ የቆይታ ጊዜን ወደ ሦስት ወራት ማሳጠሩን ትላንት ይፋ አድርጓል። ይህ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ሀገራት መካከል ናይጄርያ እና ጋና ይገኙበታል።
#USEmbassyAddisAbaba #BBCAmharic
@tikvahethiopia
" የቪዛው የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር አጥሯል ፤ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትም ተከልክሏል " - ኤምባሲው
የአሜሪካ ኤምባሲ ለኢትዮጵያውያን የሚሰጠው ቪዛ የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ማጠሩን አስታውቋል።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስደተኛ ባልሆኑ የቪዛ አመልካቾች ላይ ባደረገው የፖሊሲ ለውጥ ምክንያት ውሳኔው መተላለፉን ኤምባሲው ገልጿል።
በአዲሱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፖሊሲ መሠረት፤ " ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለኢትዮጵውያን የሚሰጠው ቪዛ ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል እና የሦስት ወር ቆይታ " እንደሚኖረው አስታውቋል።
ኤምባሲው ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. በፊት የተሰጡ ቪዛዎች ባሉበት እንደሚቀጥሉ ገልጿል።
ለንግድ እና ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን የሚያገኙት ቪዛ "B1" እና "B2" በሚለው ምድብ ውስጥ ይካተታል።
እስካሁን በነበረው አሰራር በዚህ ምድብ ውስጥ የሚገቡ ተጓዦች የሚያገኙት ቪዛ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ነበር። በተጨማሪም የቪዛው የቆይታ ጊዜ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ያስችል ነበር።
አሁን ይፋ የተደረገው ፖሊሲ የቪዛውን የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ከማሳጠር በተጨማሪ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትን ከልክሏል።
በአዲሱ ፖሊሲ ቪዛ የሚያገኙ ተጓዦች የቆይታ ጊዜ ባይጠናቀቅም እንኳ ከአሜሪካ ከወጡ በኋላ በዚያው ቪዛ ተመልሰው መግባት አይችሉም።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለያዩ አፍሪካ አገራትን ቪዛ የቆይታ ጊዜን ወደ ሦስት ወራት ማሳጠሩን ትላንት ይፋ አድርጓል። ይህ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ሀገራት መካከል ናይጄርያ እና ጋና ይገኙበታል።
#USEmbassyAddisAbaba #BBCAmharic
@tikvahethiopia
❤1.01K😭405😡110🤔60👏37😢36🙏27🕊20🥰12😱12