#Architecture
በፍልስጤም ሀገር ለሚገነባ ትምህርት ቤት በተዘጋጀ ዓለም አቀፍ የአርክቴክቸራል ዲዛይን ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያኑ ፦
➡️ አርክቴትክት ዳንኤል ዋጁ
➡️ አርክቴርክት ቢንያም በውቀቱ
➡️ አርክቴክት ፍሬዘር አብርሃ ከ231 ተወዳዳሪ አርክቴክቶች መካከል " የጣልያንን ተወዳዳሪዎች " በመከተል የ2ኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል።
አርክቴክቶቹ " Mobile school as an emergency Response in Palestine " በተሰኘ ርዕስ በተዘጋጀው በዚህ ውድድር ከአፍሪካ ብቸኛ የደረጃ ተወዳዳሪ መሆን እንደቻሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት ለተከታታይ 5 የተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለ3 አመት ያክል የሞከሩ ሲሆን በነሱም የተለያዩ ውጤቶችን አስመዝበው እንደነበር ከ3 አመት በኋሏ ግን በአምላክ እርዳታ ለዚህ ከፍተኛ ስኬት መብቃታቸውን ገልጸዋል።
ወጣቶቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት " በሃገራችን ኢትዮጵያም ብሎም በአፍሪካ ብዙ እምቅ ችሎታ ያለቸው ወጣቶች አንዳሉም በጥቂቱ ማሳየት በመቻላችን እጅግ ደስተኞች ነን " ብለዋል።
በውድድሩ ላይ በአርክቴክቸር ሙያ የታወቁ ሎሬቶች እና ባለሙያዎች በዳኝነት ተሳትፈዋል።
ከዚህ ዓለማቀፍ ውድድር 2ኛ በመሆን በማጠናቀቃቸው የ2000 ዩሮ እና የእውቅና ሰርተፍኬት ተሸላሚ በመሆን የሃገራቸውን ስም አስጠርተዋል።
(ያሸነፉበትን ስራ ከላይ ይመልከቱ)
@tikvahethiopia
በፍልስጤም ሀገር ለሚገነባ ትምህርት ቤት በተዘጋጀ ዓለም አቀፍ የአርክቴክቸራል ዲዛይን ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያኑ ፦
➡️ አርክቴትክት ዳንኤል ዋጁ
➡️ አርክቴርክት ቢንያም በውቀቱ
➡️ አርክቴክት ፍሬዘር አብርሃ ከ231 ተወዳዳሪ አርክቴክቶች መካከል " የጣልያንን ተወዳዳሪዎች " በመከተል የ2ኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል።
አርክቴክቶቹ " Mobile school as an emergency Response in Palestine " በተሰኘ ርዕስ በተዘጋጀው በዚህ ውድድር ከአፍሪካ ብቸኛ የደረጃ ተወዳዳሪ መሆን እንደቻሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት ለተከታታይ 5 የተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለ3 አመት ያክል የሞከሩ ሲሆን በነሱም የተለያዩ ውጤቶችን አስመዝበው እንደነበር ከ3 አመት በኋሏ ግን በአምላክ እርዳታ ለዚህ ከፍተኛ ስኬት መብቃታቸውን ገልጸዋል።
ወጣቶቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት " በሃገራችን ኢትዮጵያም ብሎም በአፍሪካ ብዙ እምቅ ችሎታ ያለቸው ወጣቶች አንዳሉም በጥቂቱ ማሳየት በመቻላችን እጅግ ደስተኞች ነን " ብለዋል።
በውድድሩ ላይ በአርክቴክቸር ሙያ የታወቁ ሎሬቶች እና ባለሙያዎች በዳኝነት ተሳትፈዋል።
ከዚህ ዓለማቀፍ ውድድር 2ኛ በመሆን በማጠናቀቃቸው የ2000 ዩሮ እና የእውቅና ሰርተፍኬት ተሸላሚ በመሆን የሃገራቸውን ስም አስጠርተዋል።
(ያሸነፉበትን ስራ ከላይ ይመልከቱ)
@tikvahethiopia
❤1.63K👏620🙏51😭28🥰23🕊15😱13😢13😡13🤔7