TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Architecture

በፍልስጤም ሀገር ለሚገነባ ትምህርት ቤት በተዘጋጀ ዓለም አቀፍ የአርክቴክቸራል ዲዛይን ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያኑ ፦
➡️ አርክቴትክት ዳንኤል ዋጁ
➡️ አርክቴርክት ቢንያም በውቀቱ
➡️ አርክቴክት ፍሬዘር አብርሃ ከ231 ተወዳዳሪ አርክቴክቶች መካከል " የጣልያንን ተወዳዳሪዎች " በመከተል የ2ኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል።

አርክቴክቶቹ " Mobile school as an emergency Response in Palestine " በተሰኘ ርዕስ በተዘጋጀው በዚህ ውድድር ከአፍሪካ ብቸኛ የደረጃ ተወዳዳሪ መሆን እንደቻሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት ለተከታታይ 5 የተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለ3 አመት ያክል የሞከሩ ሲሆን በነሱም የተለያዩ ውጤቶችን አስመዝበው እንደነበር ከ3 አመት በኋሏ ግን በአምላክ እርዳታ ለዚህ ከፍተኛ ስኬት መብቃታቸውን ገልጸዋል።

ወጣቶቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት " በሃገራችን ኢትዮጵያም ብሎም በአፍሪካ ብዙ እምቅ ችሎታ ያለቸው ወጣቶች አንዳሉም በጥቂቱ ማሳየት በመቻላችን እጅግ ደስተኞች ነን " ብለዋል።

በውድድሩ ላይ በአርክቴክቸር ሙያ የታወቁ ሎሬቶች እና ባለሙያዎች በዳኝነት ተሳትፈዋል።

ከዚህ ዓለማቀፍ ውድድር 2ኛ በመሆን በማጠናቀቃቸው የ2000 ዩሮ እና የእውቅና ሰርተፍኬት ተሸላሚ በመሆን የሃገራቸውን ስም አስጠርተዋል።

(ያሸነፉበትን ስራ ከላይ ይመልከቱ)

@tikvahethiopia
1.63K👏620🙏51😭28🥰23🕊15😱13😢13😡13🤔7