" ከቤት ኪራይ እና ከዕለት ፍጆታ ተርፎ ቤት ለማግኘት 25 በመቶ መቆጠብ አንችልም " - መምህራን
🔴 " ዘጠኝ እና አስር ዓመት የስራ ልምድ ያለው መምህር 10 ሺህ ብር ገደማ ደመወዝ ነው የሚከፈለው ! "
➡️ " መቆጥብ ለማይችሉት የኪራይ ቤት ገንብቶ ለመስጠት እየተሰራ ነው " - ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
ከሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንግድ ባንክ ጋር መምህራንን ጨምሮ በከተማዋ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞችን የቤት ተጠቃሚ ያደርጋል የተባለ ስምምነት ተፈራርመው ነበር።
ስምምነቱ በአነስተኛ የወለድ መጠን በ25/75 የብድር መርሐ ግብር የሚከናወን ሲሆን 25 በመቶውን መንግሥት ሰራተኛ ይቆጥባል 75 በመቶ የባንክ ብድር ይቀርባል። ብድሩ በ20 ዓመታት የሚከፈል ነው።
ንግድ ባንክ 120 ቢሊዮን ብድር እንደሚያቀርብም ተገልጾ ነበር። ፕሮጀክቱ 3 ዓመት የግንባታ ጊዜ አንድ አመት የብድር መክፈያ እፎይታ አለው ነው የተባለው።
ነገር ግን መምህራን ይህ የተባለውን 25 በመቶ ቁጠባ የመቆጠብ አቅም እንደሌላቸው ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ የመምህራን ስብሰባ ላይ የተገኙ መምህራን " የተፈራረመው የመምህራን የቤት ቁጠባና ብድር አገልግሎት ጥሩ ቢሆንም በስምምነቱ መሰረት 25 በመቶ ቁጠባ የመቆጠብ አቅም የለንም " ብለዋል።
መምህራኑ " በኑሮ ጫና ምክንያት 25 በመቶ መቆጠብ አንችልም " ሲሉ ተናግረዋል።
" ዘጠኝ እና አስር ዓመት የስራ ልምድ ያለው መምህር 10 ሺህ ብር ገደማ ደመወዝ ነው የሚከፈለው ፤ ከዚህ ደመወዝ ላይ ለቤት መሥሪያ የሚሆን 25 በመቶ ሊቆጥብ አይችልም ፤ ሌላ አማራጭ ሊዘረጋ ይገባል " ሲሉ ጠይቀዋል።
መምህራኑ ከቤት ኪራይና ከዕለት ፍጆታ ተርፎ ቤት ለማግኘት 25 በመቶ የመቆጠብ አቅም እንደሌላቸው ገልጸው " ሌላ መፍትሄ ይፈለግልን " ብለዋ።
ለመምህራኑ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፥ " መምህራን ያነሷቸ የቤት ጥያቄዎች ትክክልና ተገቢ ናቸው " ብለዋል።
" መምህራን ከዚህ በፊት በነበረ ስብሰባ ያነሱት ጥያቄ ' ለቤት ግንባታ የሚውል በነፃ መሬት ስጡን ' የሚል ነበር ፤ በተጨማሪም ' የብድር አገልግሎት አመቻቹልን ' የሚል ጥያቄ ነበር በዚህም ብድሩ ተመቻችቷል " ሲሉ አብራርተዋል።
" 25 በመቶ መቆጠብ የሚችሉ እንዲቆጥቡ እና 75 በመቶ የብድር አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ዕድል ተመቻችቷል " ያሉት ከንቲባዋ " መቆጥብ ለማይችሉት የኪራይ ቤት ገንብቶ ለመስጠት እየተሰራ ነው " ሲሉ ተናግረዋል። #ኢፕድ
#መምህራን
@tikvahethiopia
🔴 " ዘጠኝ እና አስር ዓመት የስራ ልምድ ያለው መምህር 10 ሺህ ብር ገደማ ደመወዝ ነው የሚከፈለው ! "
➡️ " መቆጥብ ለማይችሉት የኪራይ ቤት ገንብቶ ለመስጠት እየተሰራ ነው " - ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
ከሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንግድ ባንክ ጋር መምህራንን ጨምሮ በከተማዋ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞችን የቤት ተጠቃሚ ያደርጋል የተባለ ስምምነት ተፈራርመው ነበር።
ስምምነቱ በአነስተኛ የወለድ መጠን በ25/75 የብድር መርሐ ግብር የሚከናወን ሲሆን 25 በመቶውን መንግሥት ሰራተኛ ይቆጥባል 75 በመቶ የባንክ ብድር ይቀርባል። ብድሩ በ20 ዓመታት የሚከፈል ነው።
ንግድ ባንክ 120 ቢሊዮን ብድር እንደሚያቀርብም ተገልጾ ነበር። ፕሮጀክቱ 3 ዓመት የግንባታ ጊዜ አንድ አመት የብድር መክፈያ እፎይታ አለው ነው የተባለው።
ነገር ግን መምህራን ይህ የተባለውን 25 በመቶ ቁጠባ የመቆጠብ አቅም እንደሌላቸው ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ የመምህራን ስብሰባ ላይ የተገኙ መምህራን " የተፈራረመው የመምህራን የቤት ቁጠባና ብድር አገልግሎት ጥሩ ቢሆንም በስምምነቱ መሰረት 25 በመቶ ቁጠባ የመቆጠብ አቅም የለንም " ብለዋል።
መምህራኑ " በኑሮ ጫና ምክንያት 25 በመቶ መቆጠብ አንችልም " ሲሉ ተናግረዋል።
" ዘጠኝ እና አስር ዓመት የስራ ልምድ ያለው መምህር 10 ሺህ ብር ገደማ ደመወዝ ነው የሚከፈለው ፤ ከዚህ ደመወዝ ላይ ለቤት መሥሪያ የሚሆን 25 በመቶ ሊቆጥብ አይችልም ፤ ሌላ አማራጭ ሊዘረጋ ይገባል " ሲሉ ጠይቀዋል።
መምህራኑ ከቤት ኪራይና ከዕለት ፍጆታ ተርፎ ቤት ለማግኘት 25 በመቶ የመቆጠብ አቅም እንደሌላቸው ገልጸው " ሌላ መፍትሄ ይፈለግልን " ብለዋ።
ለመምህራኑ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፥ " መምህራን ያነሷቸ የቤት ጥያቄዎች ትክክልና ተገቢ ናቸው " ብለዋል።
" መምህራን ከዚህ በፊት በነበረ ስብሰባ ያነሱት ጥያቄ ' ለቤት ግንባታ የሚውል በነፃ መሬት ስጡን ' የሚል ነበር ፤ በተጨማሪም ' የብድር አገልግሎት አመቻቹልን ' የሚል ጥያቄ ነበር በዚህም ብድሩ ተመቻችቷል " ሲሉ አብራርተዋል።
" 25 በመቶ መቆጠብ የሚችሉ እንዲቆጥቡ እና 75 በመቶ የብድር አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ዕድል ተመቻችቷል " ያሉት ከንቲባዋ " መቆጥብ ለማይችሉት የኪራይ ቤት ገንብቶ ለመስጠት እየተሰራ ነው " ሲሉ ተናግረዋል። #ኢፕድ
#መምህራን
@tikvahethiopia
😭524❤168👏122😡61💔29🤔14🙏11😱10😢10🕊6🥰5