TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ብቻ ምንም ሳይታመሙ " ታመናል " ወይም ልጃቸው / ቤተሰባቸው ሳይታመም እንደታመመ አስመስለው እርዳታ የሚጠይቁ ሰዎች በትክክል ሊረዱ የሚገባቸው ሰዎችን እንዳይረዱ ያደርጋሉ።

ከዚህ ቀደም በውሸት ገንዘብ በእርዳታ መልክ ሲሰበስቡ ስለተያዙ ሰዎች መረጃ መለዋወጣችን አይዘነጋም።

ትላንት ደግሞ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጤናማ ልጁን " የካንሰር ህመምተኛ ነው " በማለት ሲለምንበት የተገኘ ወላጅን እና ግብረ-አበሩን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አሳውቋል።

በወንጀሉ የተጠረጠረው አባት (ጃዋር አብዱላሂ) ልጁን የካንስር ህመምተኛ በመሆኑ ለማሳከም ከአዋሽ 7 ወደ አዲስ አበባ መምጣቱንና ልጁን ለማሳከም እና ለምግብ እንዲሁም ለማደሪያ መቸገሩን በመግለፅ ከግብረ-አበሩ (አህመድ ከሊፈ) ጋር በመሆን በአ/አ በተለያዩ ቦታዎች ሲለምን ቆይቷል።

ትላንት ግን አንድ የፖሊስ አባል ነገሩን ተጠራጥሮ የህክምና ማስረጃ ሲጠይቃቸው ማሳየት አልቻሉም።

ፖሊስም ይዞ ፖሊስ ጣቢያ አስገብቷቸዋል።

የህፃኑ አባት እና ግብረ አበሩ ልጁ ታማሚ እንዲመስል አንገቱ ላይ ፕላስተር ለጥፈውበት የነበረ ሲሆን ፕላስተሩ ሲነሳ አንገቱ ላይ ምንም ቁስል የለም።

ህፃኑ በፖሊስ ጣቢያ  ሲጠየቅ ጤነኛ መሆኑን ገልጿል።

#ኢትዮጵያዊ የተቸገረን ሰው መርዳት ባህሉ ነው፤ ካለው ሰው ሲለምነው ጥሎ መሄድን አያውቅም ፤ ነገር ግን በውሸት / በማጭበርበር የሚካሄድ ተግባር እውነተኛ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች እንዳይረዱ ያደርጋል።

እርዳታ ሲሰጥ የህክምና ማስረጃዎች መጠየቅ ይገባል።

@tikvahethiopia
😢391131😡78👏47🤔15🥰13😱13🕊12🙏11😭9