TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ቦትስዋና

" የሀገራችንን የሰላም እሴቶች እናስቀጥል ፤ ... እንከን የለሽ የስልጣን ሽግግር እንደሚኖር አረጋግጥላችኋለሁ " - ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ሞከዌትሲ ማሲሲ

ዱማ ቦኮ የቦትስዋና ፕሬዝደንታዊ ምርጫን ማሸነፋቸው ይፋ ሆነ።

ሞከዌትሲ ማሲሲ በምርጫው ተሸንፈዋል።

ላለፉት 58 ዓመታት በሥልጣን ላይ የቆየው ‘ የቦትስዋና ዲሞክራቲክ ፓርቲ ’ ከባድ ሽንፈት አስተናግዷል። ፓርቲውን ህዝቡ በድምጹ ቀጥቶት ሸንፈትን ተከናብቧል።

ዋናው ተቃዋሚ ፓርቲ ‘ አምብሬላ ፎር ዲሞክራቲክ ቼንጅ ’ በከፍተኛ ብልጫ አሸንፏል።

ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ሞከዌትሲ ማሲሲ ፤ ለ2ኛ የስልጣን ዘመን መመረጥ ቢፈልጉም በሰላማዊ ምርጫ መሸነፋቸውን አምነው ተቀብለዋል።

በሀገራቸው የዲሞክራሲ ሂደት ግን እጅግ ኩራት እንደተሰማቸው ገልጸዋል። ገለል ብለው በሽግግሩ ላይ እንደሚሳተፉም ጠቁመዋል።

ለተመራጩ ፕሬዜዳንትም ስልክ ደውለውላቸው በምርጫው መሸነፋቸውን አምነው " እንኳን ደስ አለህ " ብለውታል።

መላው ህዝብም በአንድነት አዲሱን የመንግሥት አስተዳደር እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል።

ሁሉም በጋራ የሀገሪቱን #የሰላም እሴቶች እንዲያስቀጥል ፤ እንዲያስከብር ጥሪ አቅበዋል።

እንከን የለሽ የስልጣን ሽግግር እንደሚኖርም አረጋግጠዋል።

ሀገሪቱን ለማገልገል ለተሰጣቸው እድልም ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት አመስግነዋል።

ቦትስዋና አፍሪካ ውስጥ በተረጋጋ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ስርዓቷ በቀዳሚነት ትጠቀሳለች።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
👏1.91K229🙏65🕊46😭24🥰21🤔13😢8😱6😡6