TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ወጣቶቻችን😭   " በሶስት ወራት ብቻ ከ6,600 በላይ ወጣቶች በህገ-ወጥ መንገድ ተሰድዋል !! " - የትግራይ የወጣቶች ጉዳይ ቢሮ በትግራይ ክልል ከተሞች በሚገኙ አውራ መንገዶች " ልጄ በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ስደት ሲሄድ በአጋቾች ተይዞ ይህንን ብር ክፈል ፣ ካልከፈልክ ትገደላለህ ብለውኛል እርዱኝ " የሚሉ በትልቅ ባነር በተቀመጠ የወጣቶች ፎቶ አስደግፈው እርዳታ የሚለሙኑ ወላጆች ተበራክተዋል። …
#ስደት🚨

" ባለፉት 15 ወራት ብቻ ከ38 ሺህ በላይ ወጣቶች ተሰደዋል ፤ ከ6 ሺህ በላይ የሚሆኑት ህይወታቸው አልፏል " - የትግራይ ስፖርትና ወጣቶች ቢሮ

🚨 " ያሉት ችግሮች ወጣቱን ተስፋ በማሳጣት ህገወጥ ስደትን እንደ ብቸኛ አማራጭ እንዲመለከት እያደረጉት ነው !  "

በትግራይ በተካሄደው አስከፊና እውዳሚ ጦርነት ምክንያት የወጣቶች ህገ-ወጥ ስደት እንግልትና ሞት በእጅጉ ተባብሶ መቀጠሉ ተነግሯል።

የፕሪቶሪያ ውል ተሟልቶ አለመፈፀሙ ፣ የመልሶ ግንባታ  ስራዎች አለመጀመራቸው ፣ ሰፊ የስራ እጦት መኖር ለህገ-ወጥ የወጣቶች ፍልሰት መባባስ ምክንያቶች ናቸው ተብለዋል።

ይህን የሰማነው የትግራይ የስፖርትና የወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ከለጋሽ ድርጅቶች በመተባበር " ህገ-ወጥ ስደት " በሚል ካዘጋጀው አንድ መድረክ ላይ ነው።

ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ የበርካታ ወጣቶች ህይወት እየነጠቀ ያለውን ህገ-ወጥ ስደት አስመልክቶ በ49 የክልሉ ወረዳዎች በተካሄደ ጥናት ባለፉት 15 ወራት ብቻ ከ38 ሺህ በላይ ወጣቶች መሰዳዳቸው ያሳያል።

ከ38 ሺህ ስደተኞች ከ6 ሺህ በላይ ባለፈው ዓመት በጉዞ እያሉ ለህልፈት ተዳርገዋል ፤ አካላቸው የጎደለ አሉ ፣ አድራሻቸው የጠፉም ብዙ ናቸው።

2017 ዓ.ም ከገባ ወዲህ ብቻ  ከ6 ሺህ በላይ ወጣቶች በህገወጥ መንገድ ተሰደዋል ከነዚሁ ደግሞ 300 ገደማ ለህልፈት ተዳርገዋል።

አደጋው የክልሉ ከፍተኛ ስጋት ወደ መሆን ተሸጋግረዋል ሲል ቢሮው አሳውቋል።

በትግራይ በጦርነቱ ምክንያት ፦
የኢኮኖሚ አውታሮች ወድመዋል ፣
የብድር አገልግሎት መስጠት እጅግ የደከመ ነው፣
ሰፊ የስራ እጦት አለ እነዚህን እና ሌሎች ችግሮች ወጣቱ ተስፋ በማሳጣት ህገወጥ ስደት እንደ ብቸኛ አማራጭ  እንዲመለከት አድርገውታል።

ይህ ከፍተኛ ችግር እንዲቀረፍ የፌደራል መንግስትና ለጋሽ ድርጅቶች ድጋፋቸው እንዲቸሩ የትግራይ ክልል ስፖርትና ወጣቶች ቢሮ ጥሪ አቅርቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
😭762103😢52🕊29👏27🙏20🤔19😱9🥰5