TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ATTENTION🚨

" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ #እርግዝናን_ይፈራሉ "

ስለኤች አይቪ/ኤድስ ስርጭት የሚሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ከጊዜ ወደጊዜ እየተቀዛቀዘ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ገልጿል።

ችግሮች ከመባባሳቸው በፊት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ አሳስቧል።

ቫይረሱ ኢትዮጵያ መግባቱ ከተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶ በተሰራው እንቅስቃሴ ብዙ ለውጦች መመዝገባቸውን አስታውሷል።

ይሁን እንጂ የተመዘገቡት ለውጦች በተወሰነ ደረጃም ቢሆን መዘናጋት እንደፈጠሩ ፤ የሚዲያዎች ተሳትፎም መቀዛቀዙን ጠቁሟል።

በአሁኑ ወቅት ኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ትኩረት የሚሹና በይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ ብቻ ትኩረት ያደረጉ ናቸው ብሏል።

እነዚህም ፦
- ሴተኛ አዳሪዎች፣
- አደንዛዥ እፅ የሚጠቀሙ ሰዎች፣
- የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች፣
- አፍላ ወጣቶች በተለይ (ከማኅበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ)፣
- የቀን ሠራተኞች፣
- ከማኅበራዊ ችግሮች ጋር ተያይዞ ተጋላጭ የሆኑት እንደሆኑ አመልክቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የስርጭት መጠኑ ከ1 በመቶ በላይ ቢሆንም ከቦታ ቦታ በፆታ፣ በኅብረተሰብ ክፍል፣ በገጠርና በከተማ ከፍተኛ ልዩነት አለው ብሏል።

በከተሞች ያለው ስርጭት በገጠር ካለው በሰባት እጥፍ እንደሚበልጥም ጠቁሟል።

ይህንን ልዩነት መሠረት ያደረገ አጠቃላይ ማኅበረሰቡን ተደራሽ የሚያደርግ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ እየተከናወነ አይደለም ብሏል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፦
° የመጠጥ ቤቶች ፣
° የጫት ቤቶች
° በሺሻ ቤቶች መስፋፋት ሌላ ተግዳሮቶች እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጿል።

" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ እርግዝናን ይፈራሉ። የወጣቶች አዲስ የመያዝ ምጣኔ ጨመረ ባይባልም እየቀነሰ አይደለም፤ ይህ በራሱ ችግር ለመኖሩ አመላካች ነው "ም ብሏል።

በተለይ በወጣቶች በኩል ሁሉን አቀፍ ሥራ ባለመሠራቱ እንደ ሀገር ዋጋ ሊያስከፍሉ የሚችሉ አጋላጭ ባሕሪያት እየተስተዋሉ መሆኑን አመልክቷል።

የኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ ጠንካራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እንደሀገር ማከናወን እንደሚጠበቅ አሳስቧል። #ኢፕድ

@tikvahethiopia
481👏121😢67😭42😡35😱31🕊31🙏27🤔21🥰20
" ከቤት ኪራይ እና ከዕለት ፍጆታ ተርፎ ቤት ለማግኘት 25 በመቶ መቆጠብ አንችልም " - መምህራን

🔴 " ዘጠኝ እና አስር ዓመት የስራ ልምድ ያለው መምህር 10 ሺህ ብር ገደማ ደመወዝ ነው የሚከፈለው ! "

➡️ " መቆጥብ ለማይችሉት የኪራይ ቤት ገንብቶ ለመስጠት እየተሰራ ነው " - ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ


ከሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንግድ ባንክ ጋር መምህራንን ጨምሮ በከተማዋ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞችን የቤት ተጠቃሚ ያደርጋል የተባለ ስምምነት ተፈራርመው ነበር።

ስምምነቱ በአነስተኛ የወለድ መጠን በ25/75 የብድር መርሐ ግብር የሚከናወን ሲሆን 25 በመቶውን መንግሥት ሰራተኛ ይቆጥባል 75 በመቶ የባንክ ብድር ይቀርባል። ብድሩ በ20 ዓመታት የሚከፈል ነው።

ንግድ ባንክ 120 ቢሊዮን ብድር እንደሚያቀርብም ተገልጾ ነበር። ፕሮጀክቱ 3  ዓመት የግንባታ ጊዜ አንድ አመት የብድር መክፈያ እፎይታ አለው ነው የተባለው።

ነገር ግን መምህራን ይህ የተባለውን 25 በመቶ ቁጠባ የመቆጠብ አቅም እንደሌላቸው ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ የመምህራን ስብሰባ ላይ የተገኙ መምህራን " የተፈራረመው የመምህራን የቤት ቁጠባና ብድር አገልግሎት ጥሩ ቢሆንም በስምምነቱ መሰረት 25 በመቶ ቁጠባ የመቆጠብ አቅም የለንም " ብለዋል።

መምህራኑ " በኑሮ ጫና ምክንያት 25 በመቶ መቆጠብ አንችልም " ሲሉ ተናግረዋል።

" ዘጠኝ እና አስር ዓመት የስራ ልምድ ያለው መምህር 10 ሺህ ብር ገደማ ደመወዝ ነው የሚከፈለው ፤ ከዚህ ደመወዝ ላይ ለቤት መሥሪያ የሚሆን 25 በመቶ ሊቆጥብ አይችልም ፤ ሌላ አማራጭ ሊዘረጋ ይገባል " ሲሉ ጠይቀዋል።

መምህራኑ ከቤት ኪራይና ከዕለት ፍጆታ ተርፎ  ቤት ለማግኘት 25 በመቶ የመቆጠብ አቅም እንደሌላቸው ገልጸው " ሌላ መፍትሄ ይፈለግልን " ብለዋ።

ለመምህራኑ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፥ " መምህራን ያነሷቸ የቤት ጥያቄዎች ትክክልና ተገቢ ናቸው " ብለዋል። 

" መምህራን ከዚህ በፊት በነበረ ስብሰባ ያነሱት ጥያቄ ' ለቤት ግንባታ የሚውል በነፃ መሬት ስጡን ' የሚል ነበር ፤ በተጨማሪም ' የብድር አገልግሎት አመቻቹልን ' የሚል ጥያቄ ነበር በዚህም ብድሩ ተመቻችቷል " ሲሉ አብራርተዋል።

" 25 በመቶ መቆጠብ የሚችሉ እንዲቆጥቡ እና 75 በመቶ የብድር አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ዕድል ተመቻችቷል " ያሉት ከንቲባዋ " መቆጥብ ለማይችሉት የኪራይ ቤት ገንብቶ ለመስጠት እየተሰራ ነው " ሲሉ ተናግረዋል። #ኢፕድ

#መምህራን

@tikvahethiopia
😭524168👏122😡61💔29🤔14🙏11😱10😢10🕊6🥰5