TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#PurposeBlack የፐርፐርዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አፈፃሚ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ በአሁን ሰዓት #አሜሪካ ሀገር እንደሚገኙ ተነግሯል። " አሜሪካ የሚገኙት ለስራ ነው " ያለው ድርጅቱ የፊታችን ሀሙስ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱና መግለጫም እንደሚሰጡ አመልክቷል። ዛሬ መግለጫ ሰጥተው የነበረው የድርጅቱ የቦርድ አባል እና የህግ አማካሪ ዶ/ር ኤርሚያስ ብርሃኑ ናቸው። ፐርፐዝ ብላክ ከቤቶቹ ግንባታ…
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ መግለጫ ሰጠ።

በቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው አ/አ #ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ መቋረጡን ተከትሎ ከሁለቱም ወገን መግለጫዎች መውጣታቸው ይታወሳል።

ቢጂአይ ኢትዮጵያ ውሉ ስለመቋረጡ ከገለጸ በኋላ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሰጠው መግለጫ ላይ በተነሱ ጉዳዮች ዙሪያ የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ህግ ክፍሉ ዳይሬክተር አቶ ነጋ ምህረቴ እንዲሁም የህግ አማካሪ የሆነው "ምህረታብ እና ጌቱ አድቮኬትስ ኤል ኤል ፒ" መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው ላይ የተነሱ ጉዳዮች ምንድናቸው ?

- የድርድር ሂደቱ 8 ወራት ፈጅቷል። ቀድመን የተፈራረምነው የቀብድ ውል ነው። የቀብድ ውሉ የጊዜ ገደቡ ሦስት ወር ቢሆንም በእኛ በኩል በቅንነት 8 ወራት ጠብቀናል።

- ቀብድ ውሉን ከተፈራረምን በኋላ በእኛ በድርጅታችን ኃላፊ ጭምር እንዲሁም የመክፈል አቅም እንዳላቸው በተደጋጋሚ ማስረጃ እንዲሰጡን ብንጠይቅም እንከፍላለን ከሚል ደብዳቤ በስተቀር የሚጠበቅባቸውን ብር ለመክፈል አቅም እንዳላቸው ማስረጃ ማቅረብ አልቻሉም።

- ግብር ለመክፈል ወደኋላ የምንል አይደለንም። የሚሸጠውም ህንጻ እዳ ያለበት አይደለም ቢጂአይ እዳ ያለበት ንብረት ለሽያጭ አያቀርብም።

- ካፒታል ጌን ኪሊራንስ ለማውጣት በቅድሚያ የሽያጭ ውል መሟላት አለበት። ይህ በሌለበት ሁኔታ ክሊራንስ ማውጣት አንችልም። ይህ በህጉ የተቀመጠ የታወቀ አሰራር ነው። ቢጂአይ ክሊራንስ ለማምጣት ዝግጁ ቢሆንም ነን በቀብድ ውሉ በተጠቀሰው መሰረት በቅደም ተከተል በተቀመጠው መሰረት የሽያጭ ውሉ ላይ መስማማት ያስፈልጋል። የተለያዩ ውይይቶች ቢደረግም እሱን መፈረም አልቻሉም።

- በቀብድ ውሉ መሰረት የተከፈለው 1 ቢሊዮን ብር +15 VAT ሲሆን ቀጣዩን ክፍያ ለመክፈል የሽያጭ ውሉን መፈረም እንዲሁም በውልና ማስረጃ ሌሎች የሚያስፈልጉ ዶክመንቶች ቀርቦ እንዲጸድቅ ይጠበቃል። ይህንን ለማድረግ ከሚያስፈልገው አንዱ የሽያጭ ውል ሲሆን ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ይህንን መፈረም ባለመቻሉ ውሉን ለማቋረጥ ተገደናል።

- ከፐርፐዝ ብላክ ጋር ያለን ውል ተቋርጧል። ዳግም ተመልሰን የምንደራደርበት ነገር የለም። ይህ ውል ከተጠናቀቀ በኋላ ህንጻውን የመሸጥ አሁንም ፍላጎት አለን።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
211😱29🙏13😢11😡11😭10🕊8🥰5👏3