#DigitalEthiopia
ዛሬ " የዲጂታል ኢትዮጵያ " የግምገማ መድረክ በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ተካሂዷል።
ጠ/ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ የፌደራል እንዲሁም የክልል ከፍተኛ አመራሮች እና የዘርፉ ተዋናዮች በመድረኩ ተሳታፊ ነበሩ።
የ " ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 " ስትራቴጂ በዋናነት የዲጂታል መሰረተ ልማት በመገንባት እና በማስፋት የአገሪቱን ምጣኔ ኃብታዊ እድገት ማፋጠንን ዓላማ ያደረገ ሲሆን በአምስት ዓመታት ውስጥ ለመተግበር የታቀደ ነው።
ዛሬ ላይ የስትራቴጂውን የ4 አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል።
- ዲጂታል ሊትረሲን ለማስፋት፤
- የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎቱን የማሳደግ
- የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፤
- የዲጂታል ክፍያ ሥርዓትና የሳይበር ጥበቃ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች በሚመለከታቸው የመንግሥት ኃላፊዎች ገለጻ ተደርጎባቸዋል።
በዚህ መድረክ በቅርቡ በንግድ ባንክ ላይ ያጋጠመው ጉዳይ በስፋት እንደማሳያ ሲቀርብ ነበር።
ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የብሔራዊ ባንክ ገዢው አቶ ማሞ ምህረቱም አስተያየት ሰጥተው ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን አሉ?
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ፥ " በሳይበር ጥቃት በ2022 በዓለም ላይ 9 ትሪሊዮን ዶላር በጠላፊዎች ተመዝብሯል" ብለዋል።
" ይህ ያጋጠመው ችግር ሰዎች አቅደው አምሯቸውን ተጠቅመው ለማለት ያስቸግራል፤ ከውስጥ ያሉ ሰዎች የፈጠሩት ችግር ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ይሄ ማለት [የሳይበር ጥቃት] አይከሰትም ግን ማለት አይደለም። በሺዎች የሚቆጠሩ አታኮች በየቀኑ ተቋሞቻችን ላይ ይፈጸማሉ፤ ኢንሳ ብትመጡ ይሄንን ትመለከታላችሁ " ብለዋል።
የብሔራዊ ባንክ ገዢው ምን አሉ?
አቶ ማሞ ምህረቱ " የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ችግር በውስጥ ሰዎች የተፈጠረ ነው [ Human Error] ነው " ብለዋል።
" በዚሁ አጋጣሚ የፋይናንስ ሥርዓቱ ግልጽ ነው። ምን አይነት ገንዘብ የት እንደተላከ ከየት እንደወጣ የት እንደገባ ይታወቃል። በእንደዚህ አይነት ስህተቶች የሚጠፋ ገንዘብ አይኖርም " ሲሉ ተደምጠዋል።
" አሁን ላይ 80 በመቶ የወጣው ገንዘብ ተመላሽ ተደርጋል " ብለዋል።
ብሔራዊ ባንክ የዚህን ክስተት ሙሉ የምርመራ ውጤት በሳምንት ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግም ገልጸዋል።
#AddisAbabaTikvahFamily
@tikvahethiopia
ዛሬ " የዲጂታል ኢትዮጵያ " የግምገማ መድረክ በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ተካሂዷል።
ጠ/ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ የፌደራል እንዲሁም የክልል ከፍተኛ አመራሮች እና የዘርፉ ተዋናዮች በመድረኩ ተሳታፊ ነበሩ።
የ " ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 " ስትራቴጂ በዋናነት የዲጂታል መሰረተ ልማት በመገንባት እና በማስፋት የአገሪቱን ምጣኔ ኃብታዊ እድገት ማፋጠንን ዓላማ ያደረገ ሲሆን በአምስት ዓመታት ውስጥ ለመተግበር የታቀደ ነው።
ዛሬ ላይ የስትራቴጂውን የ4 አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል።
- ዲጂታል ሊትረሲን ለማስፋት፤
- የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎቱን የማሳደግ
- የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፤
- የዲጂታል ክፍያ ሥርዓትና የሳይበር ጥበቃ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች በሚመለከታቸው የመንግሥት ኃላፊዎች ገለጻ ተደርጎባቸዋል።
በዚህ መድረክ በቅርቡ በንግድ ባንክ ላይ ያጋጠመው ጉዳይ በስፋት እንደማሳያ ሲቀርብ ነበር።
ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የብሔራዊ ባንክ ገዢው አቶ ማሞ ምህረቱም አስተያየት ሰጥተው ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን አሉ?
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ፥ " በሳይበር ጥቃት በ2022 በዓለም ላይ 9 ትሪሊዮን ዶላር በጠላፊዎች ተመዝብሯል" ብለዋል።
" ይህ ያጋጠመው ችግር ሰዎች አቅደው አምሯቸውን ተጠቅመው ለማለት ያስቸግራል፤ ከውስጥ ያሉ ሰዎች የፈጠሩት ችግር ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ይሄ ማለት [የሳይበር ጥቃት] አይከሰትም ግን ማለት አይደለም። በሺዎች የሚቆጠሩ አታኮች በየቀኑ ተቋሞቻችን ላይ ይፈጸማሉ፤ ኢንሳ ብትመጡ ይሄንን ትመለከታላችሁ " ብለዋል።
የብሔራዊ ባንክ ገዢው ምን አሉ?
አቶ ማሞ ምህረቱ " የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ችግር በውስጥ ሰዎች የተፈጠረ ነው [ Human Error] ነው " ብለዋል።
" በዚሁ አጋጣሚ የፋይናንስ ሥርዓቱ ግልጽ ነው። ምን አይነት ገንዘብ የት እንደተላከ ከየት እንደወጣ የት እንደገባ ይታወቃል። በእንደዚህ አይነት ስህተቶች የሚጠፋ ገንዘብ አይኖርም " ሲሉ ተደምጠዋል።
" አሁን ላይ 80 በመቶ የወጣው ገንዘብ ተመላሽ ተደርጋል " ብለዋል።
ብሔራዊ ባንክ የዚህን ክስተት ሙሉ የምርመራ ውጤት በሳምንት ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግም ገልጸዋል።
#AddisAbabaTikvahFamily
@tikvahethiopia
😡457❤231👏22🙏19😭13🥰9😱7🕊5🤔2😢2