#Ethiopia #US
አሜሪካ ከ #አማራ_ፋኖ ታጣቂዎች ጋር የሰላም ንግግር እንዲጀመር የኢትዮጵያ መንግሥትን እንደጠየቀች አሳውቃለች።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ እንዲሁም የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሃመር በኦንላይን መግለጫ ሰጥተው ነበር።
መግለጫቸው ባለፉት ቀናት በኢትዮጵያ የነበራቸውን የስራ ቆይታ የተመለከተ ነበር።
በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ጨምሮ ከተለያዩ ባለስልጣናትና የተቋማት መሪዎች ጋር በኢትዮጵያ ያሉ ግጭቶች #በውይይት እንዲፈቱ መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።
አሜሪካ በኦሮሚያ እየተካሄደ ያለው ግጭት እልባት እንዲያገኝ የበኩሏን ሚና እየተጫወተች መሆኑን ገልጸው በአማራ ክልልም ግጭቶች በሰላም እንዲቋጩ ከፋኖ ጋር ንግግር እንዲጀመር ጥሪ መቅርቡን ተናግረዋል።
አምባሳደር ማይክ ሃመር ምን አሉ ?
" ባለፈው ሕዳር ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር በዳሬሰላም በተደረገው ውይይት ላይ በቀጥታ ተሳትፈናል። አሁን ይህን ለመቀጠል ዝግጁ ነን። ግጭቱ በሰላም እንዲፈታ እንዴት መመቻቸት እንደሚቻል ለሁለቱም አካላት ሃሳብ አቅርበናል።
ከፋኖ ጋር ንግግር እንዲደረግ አምባሳደር ማሲንጋ ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን እናውቃለን።
ሰላምን ለማረጋገጥ ያሉትን እድሎች በመጠቀም ጥረታችንን ለመቀጠል ዝግጁ ነን። በተደጋጋሚ እንዳልነው ለነዚህ ግጭቶች ወታደራዊ መፍትሄ አማራጭ አይሆንም አሁንም ትኩረት መደረግ ያለበት ውይይት ላይ ነው። " ብለዋል።
ሞሊ ፊ ምን አሉ ?
" ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያጋጠሟትን ፈተናዎች በሰላም ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ቁርጠንኝነታቸው እንዲቀጥሉ እናበረታታለን።
በታጣቂዎች ለሚፈፀሙት ጥቃቶች የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚወስዱት እርምጃ አሳሳቢነት ገልጸናል። የጸጥታው ሁኔታን አሳሳቢነት ብንረዳም የሲቪሎችን መብት ለመጠበቅ ተጨማሪ ጥሪ ያስፈልጋል " ብለዋል።
አምባሳደር ማይክ ሃመር ፤ " ከተለያዩ ባለስልጣናት ጋር በተደረገው ስብሰባ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር ውይይት ለማመቻቸት እንዲሁም የቀጠሉትን ግጭቶች በሰላም ለመፍታት ከአማራ ፋኖ ጋር ሊደረግ የሚችል ንግግር ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳለን ገልጸናል " ብለዋል።
ሃመር በኢትዮጵያ ላለው ግጭት ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለ ገልጸው የኢትዮጵያ መንግሥትም ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁነት እንዳለው መግለፁን እናደንቃለን ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከዚህ ቀደም ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ፅኑ አቋም እንዳለው መግለፁ ይታወቃል። ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋርም በይፋ ሁለት ጊዜ ድርድር ቢቀመጥም መጨረሻ ላይ መሳካት አልቻለም። በአማራ በኩል ከፋኖ ጋር ለድርድር ስለመቀመጥ እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።
አሜሪካውያኑ ባለስልጣናት በሰጡት መግለጫ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር ሳይሳካ ቀርቶ የተቋረጠው ድርድር መቼ እንደሚቀጥል እንዲሁም መንግሥት ከፋኖ ጋር ለድርድር ይቀመጥ እንደሆነ በግልፅ ባይናገሩም የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁ እንደሆነ እንዳሳወቃቸው ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ / ጋዜጠና ኬኔዲ አባተ መሆኑን ያሳውቃል።
@tikvahethiopia
አሜሪካ ከ #አማራ_ፋኖ ታጣቂዎች ጋር የሰላም ንግግር እንዲጀመር የኢትዮጵያ መንግሥትን እንደጠየቀች አሳውቃለች።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ እንዲሁም የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሃመር በኦንላይን መግለጫ ሰጥተው ነበር።
መግለጫቸው ባለፉት ቀናት በኢትዮጵያ የነበራቸውን የስራ ቆይታ የተመለከተ ነበር።
በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ጨምሮ ከተለያዩ ባለስልጣናትና የተቋማት መሪዎች ጋር በኢትዮጵያ ያሉ ግጭቶች #በውይይት እንዲፈቱ መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።
አሜሪካ በኦሮሚያ እየተካሄደ ያለው ግጭት እልባት እንዲያገኝ የበኩሏን ሚና እየተጫወተች መሆኑን ገልጸው በአማራ ክልልም ግጭቶች በሰላም እንዲቋጩ ከፋኖ ጋር ንግግር እንዲጀመር ጥሪ መቅርቡን ተናግረዋል።
አምባሳደር ማይክ ሃመር ምን አሉ ?
" ባለፈው ሕዳር ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር በዳሬሰላም በተደረገው ውይይት ላይ በቀጥታ ተሳትፈናል። አሁን ይህን ለመቀጠል ዝግጁ ነን። ግጭቱ በሰላም እንዲፈታ እንዴት መመቻቸት እንደሚቻል ለሁለቱም አካላት ሃሳብ አቅርበናል።
ከፋኖ ጋር ንግግር እንዲደረግ አምባሳደር ማሲንጋ ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን እናውቃለን።
ሰላምን ለማረጋገጥ ያሉትን እድሎች በመጠቀም ጥረታችንን ለመቀጠል ዝግጁ ነን። በተደጋጋሚ እንዳልነው ለነዚህ ግጭቶች ወታደራዊ መፍትሄ አማራጭ አይሆንም አሁንም ትኩረት መደረግ ያለበት ውይይት ላይ ነው። " ብለዋል።
ሞሊ ፊ ምን አሉ ?
" ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያጋጠሟትን ፈተናዎች በሰላም ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ቁርጠንኝነታቸው እንዲቀጥሉ እናበረታታለን።
በታጣቂዎች ለሚፈፀሙት ጥቃቶች የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚወስዱት እርምጃ አሳሳቢነት ገልጸናል። የጸጥታው ሁኔታን አሳሳቢነት ብንረዳም የሲቪሎችን መብት ለመጠበቅ ተጨማሪ ጥሪ ያስፈልጋል " ብለዋል።
አምባሳደር ማይክ ሃመር ፤ " ከተለያዩ ባለስልጣናት ጋር በተደረገው ስብሰባ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር ውይይት ለማመቻቸት እንዲሁም የቀጠሉትን ግጭቶች በሰላም ለመፍታት ከአማራ ፋኖ ጋር ሊደረግ የሚችል ንግግር ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳለን ገልጸናል " ብለዋል።
ሃመር በኢትዮጵያ ላለው ግጭት ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለ ገልጸው የኢትዮጵያ መንግሥትም ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁነት እንዳለው መግለፁን እናደንቃለን ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከዚህ ቀደም ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ፅኑ አቋም እንዳለው መግለፁ ይታወቃል። ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋርም በይፋ ሁለት ጊዜ ድርድር ቢቀመጥም መጨረሻ ላይ መሳካት አልቻለም። በአማራ በኩል ከፋኖ ጋር ለድርድር ስለመቀመጥ እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።
አሜሪካውያኑ ባለስልጣናት በሰጡት መግለጫ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር ሳይሳካ ቀርቶ የተቋረጠው ድርድር መቼ እንደሚቀጥል እንዲሁም መንግሥት ከፋኖ ጋር ለድርድር ይቀመጥ እንደሆነ በግልፅ ባይናገሩም የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁ እንደሆነ እንዳሳወቃቸው ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ / ጋዜጠና ኬኔዲ አባተ መሆኑን ያሳውቃል።
@tikvahethiopia
😡642❤328🕊158👏76🙏35😱18😢9🥰7😭5
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ጥያቄ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ምን ነበር ? ከትግራይ ወደ አ/አ የመጡ የማህበረሰቡ ተወካዮችና እዚህም ያሉ ተወላጆች ከጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ የትግራይ ህዝብ ከማንም ህዝብ ጋር መጋጨት እንደማይፈልግ ገልጸው ፓለቲከኞችም ልጓም ማበጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፅንኦት በጦርነቱ ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወደ ቦታቸው…
#ትግራይ #አማራ
" እኔ #ከሪፈረንደም ውጭ መፍትሄ ያለ አይመስለኝም " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በትግራይ እና አማራ በኩል ላለው ችግር " ዘላቂው መፍትሄ ህዝባዊ ሪፈረንደም " ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ጠቅለይ ሚኒስትሩ ፥ ከዚህ ቀደምም በትግራይ እና አማራ ላለው ችግር ዘላቂ መፍትሄ " ህዝቡ ህዝበ ውሳኔ ሲያደርግ " እንደሆነ በተደጋጋሚ እንደተናገሩት ጠቁመዋል።
" የሆነን ሰዎች እዛ ተቀምጠው ፣ እዛ ተቀምጠው ሲናገሩ አይደለም። ህዝቡን መልሰን ህጋዊ በሆነ መንገድ ዓለም እያየው ሪፈረንደም አድርገው ወደሚፈልጉት ቢጠቃለሉ ከዚያ በኃላ ለጥያቄ አይመችም " ብለዋል።
" አሁን ላይ ግን ሪፈረንደም የሚባል ነገር አይፈልገም " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " እራሱ ነዋሪው ሳይሆን ሌላ ሰው ነው መወሰን የሚፈልገው እዚህ እየመጣ ጥያቄ ያቀርባል ' አልተፈታም ' እያለ እኔ ደግሞ አቅጣጫ አስቀምጫለሁ እንዲፈታ " ሲሉ ተናግረዋል።
እሳቸው ያስቀመጡት አቅጣጫ በመጀመሪያ የተፈናቀውለው ህዝብ እንዲመለስ ከዛ ህዝቡ እንዲወስን (ሪፈረንደም እንዲያደርግ) መሆኑን ተናግረዋል።
" ሪፈረንደም ከተደረገ በኃላ ህዝቡ የወሰነውን እናክብርለት ፤ እኔ እዚህ ሆኜ መወሰን አልችልም " ብለዋል።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ " በትግራይ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን እና በአማራ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን በጣም የተራራቀ ነው ምንም የተቀራረበ አይደለም ለማቀራረብ የሚቻለው ህዝቡ እራሱ ሲወስን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ከዚህ (ሪፈረንደም) ውጭ ለጊዜው ሌላ #መፍትሄ ያለ እንደማይመስላቸውም ገልጸዋል።
" ህዝቡ እንዲወስን ከተደረገ የተረጋጋ አካባቢ ይፈጠራል " ብለዋል።
" እያባላን ያለው የቦታ ችግር አይደለም እኛን የሚያባላን እንደ ንብ ቀፎ ውስጣችን የሚጮኸው ጩኸት ነው እንጂ ሀገሩማ በቂ ነው ቢሰራበት ቦታዎቹ ክፍት ናቸው መንገድ የላቸው ፣ ቤት የላቸው ክፍት ናቸው ' አልገባሁም ገባሁ ' እንጨቃጨካለን እንጂ የቦታ ችግር የለም ቦታው ላይ የሚስራት ችግር ነው የሚያጨቃጭቀን " ብለዋል።
@tikvahethiopia
" እኔ #ከሪፈረንደም ውጭ መፍትሄ ያለ አይመስለኝም " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በትግራይ እና አማራ በኩል ላለው ችግር " ዘላቂው መፍትሄ ህዝባዊ ሪፈረንደም " ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ጠቅለይ ሚኒስትሩ ፥ ከዚህ ቀደምም በትግራይ እና አማራ ላለው ችግር ዘላቂ መፍትሄ " ህዝቡ ህዝበ ውሳኔ ሲያደርግ " እንደሆነ በተደጋጋሚ እንደተናገሩት ጠቁመዋል።
" የሆነን ሰዎች እዛ ተቀምጠው ፣ እዛ ተቀምጠው ሲናገሩ አይደለም። ህዝቡን መልሰን ህጋዊ በሆነ መንገድ ዓለም እያየው ሪፈረንደም አድርገው ወደሚፈልጉት ቢጠቃለሉ ከዚያ በኃላ ለጥያቄ አይመችም " ብለዋል።
" አሁን ላይ ግን ሪፈረንደም የሚባል ነገር አይፈልገም " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " እራሱ ነዋሪው ሳይሆን ሌላ ሰው ነው መወሰን የሚፈልገው እዚህ እየመጣ ጥያቄ ያቀርባል ' አልተፈታም ' እያለ እኔ ደግሞ አቅጣጫ አስቀምጫለሁ እንዲፈታ " ሲሉ ተናግረዋል።
እሳቸው ያስቀመጡት አቅጣጫ በመጀመሪያ የተፈናቀውለው ህዝብ እንዲመለስ ከዛ ህዝቡ እንዲወስን (ሪፈረንደም እንዲያደርግ) መሆኑን ተናግረዋል።
" ሪፈረንደም ከተደረገ በኃላ ህዝቡ የወሰነውን እናክብርለት ፤ እኔ እዚህ ሆኜ መወሰን አልችልም " ብለዋል።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ " በትግራይ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን እና በአማራ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን በጣም የተራራቀ ነው ምንም የተቀራረበ አይደለም ለማቀራረብ የሚቻለው ህዝቡ እራሱ ሲወስን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ከዚህ (ሪፈረንደም) ውጭ ለጊዜው ሌላ #መፍትሄ ያለ እንደማይመስላቸውም ገልጸዋል።
" ህዝቡ እንዲወስን ከተደረገ የተረጋጋ አካባቢ ይፈጠራል " ብለዋል።
" እያባላን ያለው የቦታ ችግር አይደለም እኛን የሚያባላን እንደ ንብ ቀፎ ውስጣችን የሚጮኸው ጩኸት ነው እንጂ ሀገሩማ በቂ ነው ቢሰራበት ቦታዎቹ ክፍት ናቸው መንገድ የላቸው ፣ ቤት የላቸው ክፍት ናቸው ' አልገባሁም ገባሁ ' እንጨቃጨካለን እንጂ የቦታ ችግር የለም ቦታው ላይ የሚስራት ችግር ነው የሚያጨቃጭቀን " ብለዋል።
@tikvahethiopia
❤1K😡556👏89🕊79🤔46😱18🥰17😢16🙏15😭8
TIKVAH-ETHIOPIA
#አብና🕯 " የ4ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል ፤ የ6 ሰዎች አስከሬን ሊገኝ አልቻለም ! " በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ ልዩ ስሙ ኖላ በተባለ ቦታ ነሐሴ 18/2016 ዓ.ም በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ 10 ሰዎች ሞተዋል። የጠለምት ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ተስፋየ ወርቅነህ ምን አሉ ? " የ4 ሰዎች አስከሬን በፍለጋ ተገኝቷል ፤ የቀሪ 6…
#አማራ #ጎንደር🕯
በአማራ፣ ሰሜን ጎንደር ዞን 3 ወረዳዎች በመሬት መንሸራተት አደጋ የሞቱ እና የተጎዱ ሰዎች ቁጥር በዛሬው ዕለት ጨምሯል።
ሟች ወገኖቻችን 23 ደርሰዋል።
የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖቻችን ደግሞ 8 መድረሳቸው ተነግሯል።
ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወገኖቻችን አጠቃላይ ከ2 ሺህ 700 በላይ ናቸው።
አደጋው የደረሰው በዞኑ በጠለምት፣ በጃናሞራ፣ በአዲአርቃይና በየዳ ወረዳዎች በሚገኙ 11 የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ ነው፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሰሜን ጎንደር ኮሚኒኬሽን ነው።
#አማራ #ሰሜንጎንደር
@tikvahethiopia
በአማራ፣ ሰሜን ጎንደር ዞን 3 ወረዳዎች በመሬት መንሸራተት አደጋ የሞቱ እና የተጎዱ ሰዎች ቁጥር በዛሬው ዕለት ጨምሯል።
ሟች ወገኖቻችን 23 ደርሰዋል።
የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖቻችን ደግሞ 8 መድረሳቸው ተነግሯል።
ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወገኖቻችን አጠቃላይ ከ2 ሺህ 700 በላይ ናቸው።
አደጋው የደረሰው በዞኑ በጠለምት፣ በጃናሞራ፣ በአዲአርቃይና በየዳ ወረዳዎች በሚገኙ 11 የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ ነው፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሰሜን ጎንደር ኮሚኒኬሽን ነው።
#አማራ #ሰሜንጎንደር
@tikvahethiopia
😢1.4K😭551❤93🙏48🕊41😱32🤔19👏15🥰9