#ጥቆማ
ከ3500 ዶላር እስከ 10 ሺ ዶላር የሚያሸልመው ለግብርና መሻሻል የሚረዱ የቴክኖሎጂ ውድድር መጀመሩን " አዩቲ ኢትዮጵያ ቻሌንጅ " ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
ሄፈር ኢንተርናሽናል የውድድሩ አዘጋጅ ባሳወቀው መሠረት፣ የውድድሩ ዓላማ የአርሶ አደሮች ምርታማነትን መጨመር የሚያስችሉ፣ ድካም የሚቀንሱ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሀሳብ ማቅረብ ነው።
ወድድሩ ሲካሄድ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የሚወዳደሩት ከ18 - 30 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንደሆኑና ተገልጿል።
የፈጠራ ሀሳባቸውን በ #ኦንላይን ማስገባት እንዳለባቸው ተመላክቷል።
የውድድሩ አሸናፊዎች በምን መልኩ ይለያሉ ?
➡️ ተወዳዳሪዎቹ ከሚያቀርቧቸው የቴክኖሎጂ ሀሳቦች 30ዎቹ በዳኞች ይመርጣሉ፣
➡️ ዳኞች በተገኙበት 30ዎቹ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ፣
➡️ ከ30ዎቹ 10 ሀሳቦችን ዳኞች ይመርጣሉ፣
➡️ 10ሩ ተወዳዳሪዎች ለ10 ቀናት ይሰለጥናሉ፣
➡️ ከስልጠናው በኋላ የመጨረሻ የ3 ተወዳዳሪዎች ሀሳብ ይመረጣል።
የሽልማት አሰጣጡ በምን መልኩ ነው ?
1ኛ ለወጣው 10 ሺህ ዶላር፣
2ኛ ለወጣው 6 ሺህ 500 ዶላር፣
3ኛ ለወጣው ሀሳብ ደግሞ 3 ሺህ 500 ዶላር የሥራ ማስጀመሪያ እና የማበረታቻ ሽልማት ይደረግላቸዋል።
ከዚህ ቀደም በተካሄዱት 2 ውድድሮች የተለያዩ የግብርና ዘርፍ ላይ ያተኮሩ አጠቃላይ 12 የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ተግባር ላይ መዋላቸው ተነግሯል።
ማመልከቻ ፦ https://ayute-ethiopia.et/apply-here/
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@TikvahEthiopia
ከ3500 ዶላር እስከ 10 ሺ ዶላር የሚያሸልመው ለግብርና መሻሻል የሚረዱ የቴክኖሎጂ ውድድር መጀመሩን " አዩቲ ኢትዮጵያ ቻሌንጅ " ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
ሄፈር ኢንተርናሽናል የውድድሩ አዘጋጅ ባሳወቀው መሠረት፣ የውድድሩ ዓላማ የአርሶ አደሮች ምርታማነትን መጨመር የሚያስችሉ፣ ድካም የሚቀንሱ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሀሳብ ማቅረብ ነው።
ወድድሩ ሲካሄድ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የሚወዳደሩት ከ18 - 30 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንደሆኑና ተገልጿል።
የፈጠራ ሀሳባቸውን በ #ኦንላይን ማስገባት እንዳለባቸው ተመላክቷል።
የውድድሩ አሸናፊዎች በምን መልኩ ይለያሉ ?
➡️ ተወዳዳሪዎቹ ከሚያቀርቧቸው የቴክኖሎጂ ሀሳቦች 30ዎቹ በዳኞች ይመርጣሉ፣
➡️ ዳኞች በተገኙበት 30ዎቹ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ፣
➡️ ከ30ዎቹ 10 ሀሳቦችን ዳኞች ይመርጣሉ፣
➡️ 10ሩ ተወዳዳሪዎች ለ10 ቀናት ይሰለጥናሉ፣
➡️ ከስልጠናው በኋላ የመጨረሻ የ3 ተወዳዳሪዎች ሀሳብ ይመረጣል።
የሽልማት አሰጣጡ በምን መልኩ ነው ?
1ኛ ለወጣው 10 ሺህ ዶላር፣
2ኛ ለወጣው 6 ሺህ 500 ዶላር፣
3ኛ ለወጣው ሀሳብ ደግሞ 3 ሺህ 500 ዶላር የሥራ ማስጀመሪያ እና የማበረታቻ ሽልማት ይደረግላቸዋል።
ከዚህ ቀደም በተካሄዱት 2 ውድድሮች የተለያዩ የግብርና ዘርፍ ላይ ያተኮሩ አጠቃላይ 12 የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ተግባር ላይ መዋላቸው ተነግሯል።
ማመልከቻ ፦ https://ayute-ethiopia.et/apply-here/
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@TikvahEthiopia
👏182❤76🕊11😡11😱7😢7🥰4🙏4