TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba #Exam ለአዲስ አበባ አስተዳደር አመራሮች ፣ ባለሞያዎች / ሠራተኞች የተሰጠውን የቴክኒክ እና ባህሪ ብቃት ፈተና የማለፊያ ነጥብ አምጥተው ያለፉ #የክዋኔ_ክህሎት ስልጠና ይሰጣቸዋል ተብሏል። የማለፊያ ነጥብ ማምጣት ሳይችሉ ቀርተው #ያላለፉት ደግሞ #የአቅም_ግንባታ_ስልጠና እንደሚሰጣቸው ተጠቁሟል። በተጨማሪ የማለፊያ ውጤት ያላመጡት ዝቅ ብለው እንደሚመደቡ ፤ አሁን ላይ #ስንብት…
#አዲስአበባ

ዛሬ 3,854 የመንግሥት ሰራተኞች ፈተና ተቀምጠዋል።

ዛሬ ለባህሪና ብቃት ምዘና ፈተና የተቀመጡት ፦
- የአዲስ አበባ መሬት ይዞታ ቢሮ፣
- የመሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ
- የከንቲባ ፅ/ቤት (ማለትም የ3 ተቋማት) ዳይሬክተሮች፣ ቡድን መሪዎች፣ ሰራተኞች እና ባለሙያዎች ናቸው።

ፈተናው በአዲስ አበባ ዩኒቪርስቲ በ6 ኪሎ ካምፓስ ውስጥ እየተሰጠ ይገኛል።

ከዚህ ቀደም 15,151 የአስተዳደሩ አመራሮች፣ ሠራተኞች / ባለሞያዎች (የ13 ተቋማት) የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና መውሰዳቸውና ውጤቱም ይፋ መደረጉ ይታወሳል።

ፈተናውን ከወሰዱ 4,213 አመራሮች ያለፉት 1,422 መሆናቸው እንዲሁም ፈተናውን ከወሰዱ 10,257 ባለሞያዎች / ሠራተኞች ያለፉት 5,095 መሆናቸው መገለፁ አይዘነጋም።

የማለፊያ ነጥብ አምጥተው ላለፉ የክዋኔ ክህሎት ስልጠና እንደሚሰጥ ፤ የማለፊያ ነጥብ ማምጣት ሳይችሉ ቀርተው ያላለፉት ደግሞ የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሚሰጣቸው መነገሩ ይታወቃል።

በተጨማሪ ፤ የማለፊያ ውጤት ያላመጡት ዝቅ ብለው እንደሚመደቡ ፤ አሁን ላይ #ስንብት የሚባል ነገር እንደሌለ ፤ ስንብት የሚፈፀመው መጨርሻ ላይ ሁሉ ነገር ከተጠናቀቀና ሌላ አማራጭ ከጠፋ ብቻ መሆኑን የከተማው አስተዳደር ማሳወቁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
😢335227😡139🙏70😭66🕊24😱22🥰20👏2