TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ቤኒሻንጉልጉሙዝ

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ወደ አዲስ አበባም ሆነ ወደ አጎራባች አካባቢዎች የሚወስደው መንገድ በፀጥታ ምክንያት ዝግ በመሆኑ፣ ለከፍተኛ ሕክምና ሪፈር የሚጻፍላቸው ሕሙማን ሕክምና ባለማግኘታቸው ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑን የአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል አስታወቀ፡፡

ከአሶሳ ከተማ ተነስቶ ወደ መተከልና ኦሮሚያ ክልል የሚወስደው መንገድ በፀጥታ ችግር ምክንያት በመዘጋቱ ሕሙማን የከፋ ችግር ውስጥ ወድቀዋል።

የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሶፊያ አወት ምን አሉ ?

- ከአጎራባች ሱዳን ፈልሰው የመጡ ስደተኞችና ምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢ የሠፈሩ ዜጎች ሙሉ ለሙሉ የሕክምና አገልግሎት የሚያገኙት አሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል በመሆኑ፣ ሆስፒታሉ አገልግሎት ለመስጠት ከአቅሙ በላይ ሆኖበታል።

- ሆስፒታሉ ከፍተኛ የሆነ የሕክምና ግብዓት እጥረት አለበት።

- ወደ ሌላ ቦታ ሄደው ሕክምና እንዲያገኙ ሪፈር የሚጽፍላቸው ሕሙማን አቅም ያላቸው ብቻ የአየር ትራንስፖርት ተጠቅመው የሕክምና አገልግሎት እያገኙ ነው።

- በክልሉ አብዛኛውን ነዋሪ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያለ ሲሆን፣ ወደ አዲስ አበባ ከተማም ሆነ ወደ ሌሎች አጎራባች አካባቢዎች በአየር ትራንስፖርት ሄደው ለመታከም የገንዘብ ችግር ስለሚገጥማቸው ሞታቸውን የሚጠባበቁበት ሁኔታ ተፈጥሯል።

- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቁጥር አንድ ከሚባሉት ሆስፒታሎች ውስጥ አንዱ ነው። በአሁኑ ወቅት በቀን ከ150 በላይ ለሆኑ ሕሙማን አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡

- ለሆስፒታሉ የሚቀርበው መድኃኒትና ሆስፒታሉ የሚሰጠው አገልግሎት ጭራሽ የማይመጣጠን ነው።

- በፀጥታ ችግር ምክንያት መድኃኒት እየቀረበ ያለው በአየር ትራንስፖርት ነው።

- በአየር ትራንስፖርት መድኃኒት ቢመጣም ቶሎ ቶሎ የሚያልቅ በመሆኑ መድኃኒት ለመግዛትም ሆነ ለመድኃኒት ማጓጓዣ ሆስፒታሉ ከፍተኛ ወጪ እያወጣ ይገኛል።

- ሆስፒታሉ የቀዶ ጥገና፣ የማዋለድ፣ የዓይን ሕክምናና ሌሎች አገልግሎቶችን ይሰጣል።

- ከዚህ በፊትም የፀጥታ ችግር ባልነበረበት ወቅት ሕሙማንን በፍጥነት በአምቡላንስ በማመላለስ አገልግሎት ይሰጥ ነበር፤ ይሁን እንጂ የፀጥታ ችግር በክልሉ በመባባሱ አምቡላንሶች እንደ ልብ ተንቀሳቅሰው አገልግሎት እንደማይሰጡ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አንድ አምቡላንስ በታጣቂ ኃይሎች መቃጠሉንና ውስጥ የነበሩ ሕሙማንና ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዓለም ደበሎ ምን አሉ ?

* በክልሉ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡ ስድስት ሆፒታሎች አሉ፡፡ ሆስፒታሎቹ የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት የግብዓት ችግር ገጥሟቸዋል።

* በክልሉ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት አገልግሎት ለመስጠት ተቸግረዋል።

* የመድኃኒትም ሆነ ሌሎች የሕክምና ግብዓቶችን በተመለከተ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር በአየር ትራንስፖርት እያስገባን ቢሆን ችግሩ ግን ከፍተኛ ነው።

* በክልሉ የሕክምና አገልግሎቶች የሚሰጡ ሆስፒታሎች ለሕሙማን ሪፈር ሲጽፉ አብዛኞቹ ሕሙማን በአየር ትራንስፖርት ሄደው ለመታከም ይቸገራሉ፤ በዚህ ምክንያት እዚያው ሕክምናቸውን ለመከታተል ተገደዋል።

ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ

@tikvahethiopia
😭22164🕊24🙏11🥰4👏1😢1