#ኢትዮጵያ #ባንኮች
የአገሪቱ ባንኮች ከአሠራር ጋር በተያያዙ ክፍተቶች በተለያዩ ሥልቶች ለሚፈጸሙ የማጭበርበር ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ እየሆኑ መምጣታቸውን ፣ ይህ ሁኔታም በቀጣይ የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ ውስጥ የበለጠ እንደሚጨምር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።
ብሔራዊ ባንክ የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ጤናማነትን በመገምገም አንድ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
ሪፖርቱ ምን ይላል ?
➡️ የአገሪቱ ባንኮች በበይነ መረብ ማጭበርበርያ ሥልቶች፣ ከባንኮች የውስጥ ሠራተኞችና ከሦስተኛ ወገን በሚደርሱባቸው የምዝበራ ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ እየተጋለጡ ናቸው።
➡️ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ማለትም እስከ ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ በሐሰተኛ ሰነዶችና በሌሎች የማጭበርበር ድርጊቶች ባንኮች 1 ቢሊዮን ብር አጥተዋል። የተመዘበሩት የገንዘብ መጠንም ከቀዳሚው ዓመት በእጥፍ ጨምሯል።
➡️ የባንክ ማጭበርበሮች በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ወደ 1 ቢሊዮን ብር ሲደርሱ፣ ከአምናው በእጥፍ አድጓል። እነዚህ ጉዳዮች የተከሰቱት በዋናነት ፦
° ሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶችንና ቼኮችን በመጠቀም ገንዘብ በማጭበርበር፣
° ያልተፈቀደ የባንክ ዋስትና በማቅረብ፣
° የተሰረቁ የኤቲኤም ካርዶችን በመጠቀም ገንዘብ በማውጣት ድርጊት
° በሐሰተኛ የስልክ ጥሪዎችና አጭር የጽሑፍ መልዕክቶችን በመጠቀም ነው። በተጠቀሱት የማጭበርበሪያ ሥልቶችም 20 ባንኮች ጉዳት ደርሶባቸዋል። በሰኔ ወር 2015 መጨረሻ ላይ 3 ባንኮች 200 ሚሊዮን ብር ተዘርፈዋል።
➡️ ባንኮች አዳዲስ ምርቶችንና አገልግሎቶችን ሲተዋወቁ በአሠራር ክፍተቶች ሳቢያ በከፍተኛ ደረጃ ለአደጋ እየተጋለጡ ናቸው።
➡️ ባንኮች ከአሠራር ጋር የተያያዙ አደጋዎችን ለመከላከልና የመጭበርበር ተጋላጭነታቸውን ለመቀነስ፣ ውጤታማ የቁጥጥር ሥልቶችንና አሠራርችን በመተግበር ላይ ሊያተኩሩ ይገባል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የ #ሪፖርተርጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የአገሪቱ ባንኮች ከአሠራር ጋር በተያያዙ ክፍተቶች በተለያዩ ሥልቶች ለሚፈጸሙ የማጭበርበር ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ እየሆኑ መምጣታቸውን ፣ ይህ ሁኔታም በቀጣይ የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ ውስጥ የበለጠ እንደሚጨምር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።
ብሔራዊ ባንክ የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ጤናማነትን በመገምገም አንድ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
ሪፖርቱ ምን ይላል ?
➡️ የአገሪቱ ባንኮች በበይነ መረብ ማጭበርበርያ ሥልቶች፣ ከባንኮች የውስጥ ሠራተኞችና ከሦስተኛ ወገን በሚደርሱባቸው የምዝበራ ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ እየተጋለጡ ናቸው።
➡️ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ማለትም እስከ ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ በሐሰተኛ ሰነዶችና በሌሎች የማጭበርበር ድርጊቶች ባንኮች 1 ቢሊዮን ብር አጥተዋል። የተመዘበሩት የገንዘብ መጠንም ከቀዳሚው ዓመት በእጥፍ ጨምሯል።
➡️ የባንክ ማጭበርበሮች በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ወደ 1 ቢሊዮን ብር ሲደርሱ፣ ከአምናው በእጥፍ አድጓል። እነዚህ ጉዳዮች የተከሰቱት በዋናነት ፦
° ሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶችንና ቼኮችን በመጠቀም ገንዘብ በማጭበርበር፣
° ያልተፈቀደ የባንክ ዋስትና በማቅረብ፣
° የተሰረቁ የኤቲኤም ካርዶችን በመጠቀም ገንዘብ በማውጣት ድርጊት
° በሐሰተኛ የስልክ ጥሪዎችና አጭር የጽሑፍ መልዕክቶችን በመጠቀም ነው። በተጠቀሱት የማጭበርበሪያ ሥልቶችም 20 ባንኮች ጉዳት ደርሶባቸዋል። በሰኔ ወር 2015 መጨረሻ ላይ 3 ባንኮች 200 ሚሊዮን ብር ተዘርፈዋል።
➡️ ባንኮች አዳዲስ ምርቶችንና አገልግሎቶችን ሲተዋወቁ በአሠራር ክፍተቶች ሳቢያ በከፍተኛ ደረጃ ለአደጋ እየተጋለጡ ናቸው።
➡️ ባንኮች ከአሠራር ጋር የተያያዙ አደጋዎችን ለመከላከልና የመጭበርበር ተጋላጭነታቸውን ለመቀነስ፣ ውጤታማ የቁጥጥር ሥልቶችንና አሠራርችን በመተግበር ላይ ሊያተኩሩ ይገባል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የ #ሪፖርተርጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
😭126❤85👏42😱25🤔19😢10🕊7🥰6😡3🙏1