TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ • " ከ13,000 በላይ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው የከፋ ችግር ውስጥ ናቸው " - የዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ፅ/ቤት • " በሰሃላ ወረዳ 94 በመቶ ነፍሰጡሮችና የሚያጠቡ እናቶች፣ 45 በመቶ ከአምስት ዓመት በታች ሕጻናት በምግብ እጥረት ተጎድተዋል " - የዞኑ ጤና መምሪያ ቢሮ በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በአበርገሌና…
#አማራ #ዋግኽምራ
" ዞኑ ከነበሩት 33 አምቡላንሶች አሁን ላይ 9 አምቡላንሶች ብቻ ነው ያሉት። … የህፃናትና የእናቶች የህክምና አገልግሎት አደጋ ውስጥ ነው " - የዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ
ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ፦
* የመድኃኒት፣
* የትራንስፖርት፣
* የሕክምና መሣሪያዎች እጥረት በማጋጠሙ በዞኑ የሚገኙ የሕክምና ተቋማት አገልግሎት ለመስጠት ፈተና እንደሆነባቸው በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ ምን አሉ ?
- ዞኑ ከነበሩት 33 አምቡላንሶች አሁን ላይ ዘጠኝ አምቡላንሶች ብቻ ነው ያሉት። በሰርቪስ፣ በሥራ ጫና ከጥቅም ውጪ ሆነዋል።
- በተፈለገና ባለቀ ሰዓት ወቅቱን ጠብቆ መድኃኒት ለመግዛት እንቅስቃሴዎች ገድበውናል። የሴኩሪቲ ችግር በጣም አሳሳቢ ነው። ሪፈራሎች በሚፈለገው መልኩ እየተንቀሳቀሱ አይደለም። ስለዚህ በእናቶችና በህፃናት የጤና አገልግሎት ጠቅላላ አደጋ ውስጥ ነው።
- ሰውከፍሎ መታከም አልቻለም። የጤና መድህን ሽፋናችን ዝቅተኛ ነው። ራሳቸውን ሰርቫይብ ማድረግ ያልቻሉ፣ ለመከላከያ፣ ለልዩ ኃይል ለሌሎች ቁስለኞች ሁሉ ጠቅላላ አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ የጤና ተቋማት ናቸው ያሉት። እየጠፉ ያሉበት ሁኔታ ነው ያለው። ግን ደግሞ በትግል እንደምንም እየተቋቋምን ማኅበረሰቡን ለማዳረስ እየሞከርን ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጸጥታው ችግር በድርቅ ለተጎዱት ምን ጉዳት አስከተለ ? ሲል ጠይቋል።
° ይህ ሁኔታ በተለይ በዞኑ በድርቅ ምክንያት ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች እያሳደረው ያለው ተፅዕኖ ከፍተኛ ነው።
* ኮሌራ ተከስቶብናል። እንደ ጤና ተቋማት ትልቅ ሥጋት፣ ከባድ ወረርሽኝ ላይ ነው ያለነው። ቁጥር አንድ ተጋላጭ የሚባሉት ህፃናት፣ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች፣ አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞች ናቸው።
° ከኅዳር 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የልየታ ሥራ በሁሉም ወረዳዎች አሰርተን ነበር። በዚያ መሠረት አስደንጋጭ ቁጥር ነው ያገኘነው። ከለየናቸው ነፍሰጡር፣ አጥቢ እናቶች 81 በመቶ የሚሆኑት አጣዳፊ መካከለኛ የምግብ እጥረት ያለባቸው ናቸው።
° እንደ ዞን ከለየናቸው ህፃናት 45 በመቶዎቹ አጣዳፊ ከፍተኛ የምግብ እጥረት ችግር ያለባቸው ናቸው። ይህ ቁጥር ከተቀመጠው ስታንዳርድ በላይና አስደንጋጭ ነው። አስደንጋጭ ከመሆኑም በላይ አሁን እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች በጣም ዘገምተኛ ናቸው ብለዋል።
የዋግኽምራ ብሄረሰብ ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፦
☑️ 95 በመቶ እናቶች በምግብ እንደተጎዱ፣
☑️ የህፃናት የረሃብ መጠን 15 በመቶ ከደረሰ እንኳ ከስታንዳርድ በላይ እንደሆነ ነገር ግን ከ30 በመቶ በላይ ህፃናት በምግብ እጥረት እንደተጎዱ ገልጾ ነበር።
አሁን የጤና መምሪያ ኃላፊው በገለጹት መሠረት ደግሞ የህፃናቱ የምግብ እጥረት ጉዳት ወደ 45 በመቶ ከፍ ብሏል።
የዞኑ ጤና መምሪያ ፤ በተለይ የጸጥታው ችግር ከድርቁ ጋር ተያይዞ በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ፈተና መሆኑን፣ ድርቅ፣ ጦርነት፣ ወረርሽኝ በዞኑ መደራረባቸውን ገልጾ እስካሁን ድጋፍ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው፣ አሁንም መንግሥት፣ በጎ አድራጊ ድርጅቶች ከችግሩ ውስብስብነት አንፃር ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተረድተው #እርዳታቸውን እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧል።
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተጠናክሮ የቀረበ ነው።
@tikvahethiopia
" ዞኑ ከነበሩት 33 አምቡላንሶች አሁን ላይ 9 አምቡላንሶች ብቻ ነው ያሉት። … የህፃናትና የእናቶች የህክምና አገልግሎት አደጋ ውስጥ ነው " - የዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ
ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ፦
* የመድኃኒት፣
* የትራንስፖርት፣
* የሕክምና መሣሪያዎች እጥረት በማጋጠሙ በዞኑ የሚገኙ የሕክምና ተቋማት አገልግሎት ለመስጠት ፈተና እንደሆነባቸው በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ ምን አሉ ?
- ዞኑ ከነበሩት 33 አምቡላንሶች አሁን ላይ ዘጠኝ አምቡላንሶች ብቻ ነው ያሉት። በሰርቪስ፣ በሥራ ጫና ከጥቅም ውጪ ሆነዋል።
- በተፈለገና ባለቀ ሰዓት ወቅቱን ጠብቆ መድኃኒት ለመግዛት እንቅስቃሴዎች ገድበውናል። የሴኩሪቲ ችግር በጣም አሳሳቢ ነው። ሪፈራሎች በሚፈለገው መልኩ እየተንቀሳቀሱ አይደለም። ስለዚህ በእናቶችና በህፃናት የጤና አገልግሎት ጠቅላላ አደጋ ውስጥ ነው።
- ሰውከፍሎ መታከም አልቻለም። የጤና መድህን ሽፋናችን ዝቅተኛ ነው። ራሳቸውን ሰርቫይብ ማድረግ ያልቻሉ፣ ለመከላከያ፣ ለልዩ ኃይል ለሌሎች ቁስለኞች ሁሉ ጠቅላላ አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ የጤና ተቋማት ናቸው ያሉት። እየጠፉ ያሉበት ሁኔታ ነው ያለው። ግን ደግሞ በትግል እንደምንም እየተቋቋምን ማኅበረሰቡን ለማዳረስ እየሞከርን ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጸጥታው ችግር በድርቅ ለተጎዱት ምን ጉዳት አስከተለ ? ሲል ጠይቋል።
° ይህ ሁኔታ በተለይ በዞኑ በድርቅ ምክንያት ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች እያሳደረው ያለው ተፅዕኖ ከፍተኛ ነው።
* ኮሌራ ተከስቶብናል። እንደ ጤና ተቋማት ትልቅ ሥጋት፣ ከባድ ወረርሽኝ ላይ ነው ያለነው። ቁጥር አንድ ተጋላጭ የሚባሉት ህፃናት፣ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች፣ አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞች ናቸው።
° ከኅዳር 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የልየታ ሥራ በሁሉም ወረዳዎች አሰርተን ነበር። በዚያ መሠረት አስደንጋጭ ቁጥር ነው ያገኘነው። ከለየናቸው ነፍሰጡር፣ አጥቢ እናቶች 81 በመቶ የሚሆኑት አጣዳፊ መካከለኛ የምግብ እጥረት ያለባቸው ናቸው።
° እንደ ዞን ከለየናቸው ህፃናት 45 በመቶዎቹ አጣዳፊ ከፍተኛ የምግብ እጥረት ችግር ያለባቸው ናቸው። ይህ ቁጥር ከተቀመጠው ስታንዳርድ በላይና አስደንጋጭ ነው። አስደንጋጭ ከመሆኑም በላይ አሁን እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች በጣም ዘገምተኛ ናቸው ብለዋል።
የዋግኽምራ ብሄረሰብ ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፦
☑️ 95 በመቶ እናቶች በምግብ እንደተጎዱ፣
☑️ የህፃናት የረሃብ መጠን 15 በመቶ ከደረሰ እንኳ ከስታንዳርድ በላይ እንደሆነ ነገር ግን ከ30 በመቶ በላይ ህፃናት በምግብ እጥረት እንደተጎዱ ገልጾ ነበር።
አሁን የጤና መምሪያ ኃላፊው በገለጹት መሠረት ደግሞ የህፃናቱ የምግብ እጥረት ጉዳት ወደ 45 በመቶ ከፍ ብሏል።
የዞኑ ጤና መምሪያ ፤ በተለይ የጸጥታው ችግር ከድርቁ ጋር ተያይዞ በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ፈተና መሆኑን፣ ድርቅ፣ ጦርነት፣ ወረርሽኝ በዞኑ መደራረባቸውን ገልጾ እስካሁን ድጋፍ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው፣ አሁንም መንግሥት፣ በጎ አድራጊ ድርጅቶች ከችግሩ ውስብስብነት አንፃር ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተረድተው #እርዳታቸውን እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧል።
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተጠናክሮ የቀረበ ነው።
@tikvahethiopia
😢214❤48😭9👏8😡7🥰5🙏5😱4🕊2
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ #ዋግኽምራ " ዞኑ ከነበሩት 33 አምቡላንሶች አሁን ላይ 9 አምቡላንሶች ብቻ ነው ያሉት። … የህፃናትና የእናቶች የህክምና አገልግሎት አደጋ ውስጥ ነው " - የዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ፦ * የመድኃኒት፣ * የትራንስፖርት፣ * የሕክምና መሣሪያዎች እጥረት በማጋጠሙ በዞኑ የሚገኙ የሕክምና ተቋማት አገልግሎት ለመስጠት ፈተና እንደሆነባቸው በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሄረሰብ…
#ዋግኽምራ
" ድርቁ በጣም እየባሰ ነው። መታከም ያለባቸው ህፃናት ለተከታታይ 2 ወራት ምንም አልተደረገላቸውም" - ዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ
በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ በዞኑ ስላሉ አሳሳቢ ጉዳዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
- ድርቁ በጣም #እየባሰ ነው። ባለፈው ጥናት ካጠናን በኋላ ሊደረግ የሚገባው ግን ያልተደረገ በጣም በስፋት ነው ያለው።
- የምግብ እጥረት እንዳለባቸው በተረጋገጠው መሠረት #ህፃናት #ነፍሰጡር፣ #አጥቢ እናቶች ወደ ተለያዩ ፕሮግራሞች ገብተው ሊደገፉ ነበር። እስቲል ማሟያ ምግብ በምንለው እጥረት እስካሁን ምንም አልተደረገላቸውም። እኛ #እየጮህን ነው። እስካሁን የመጣ፣ የተደረገ ድጋፍም የለም።
- በሌላ በኩል ድርቅ በተከሰተባችው አካባቢዎች አጠቃላይ የጤና መድህን የምንለው ፕሮግራም የአመት ክፍያው የሚያልቀው አሁን ነው። አልፎ ለማስከፈልም አልቻልንም። በጠቅላላ የጤና አገልግሎታቸው በጣም #የሚያሳዝን ሁኔታ እየገባንበት ያለንበት ሁኔታ ነው ያለው።
ምን ያህል ህፃናትና እናቶች ናቸው አሁን አስቸኳይ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው?
* በድርቅ የተጎዱት ወደ 33,000 የሚሆኑ ሰዎች ናቸው ከአንድ ወረዳ ብቻ። በአጠቃላይ እንደ ዞን በዚህ ድርቅ ተጎድተዋል ብለን የምናስባቸው ከ180,000 በላይ ህዝቦች ናቸው።
* ከእዚህ ውስጥ የሚበዙት ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች ናቸው። ወደ 7,000 ይደርሳሉ #ነፍሰጡርና አጥቢዎች ብቻ። ከአምስት ዓመት በታች #ህፃናት ኦልሞስት ወደ #18,000 አካባቢ ይደርሳሉ። እነዚህ ሁሉ አስቸኳይ ምግብ የሚፈልጉ ናቸው።
አቶ አሰፋ ታጣቂዎችን በተመለከተ ምን አሉ ?
° ታጣቂዎች የመጀመሪያ ታርጌታቸው ጤና ተቋማትን መዝርፍ ነው። እኛ አገልግሎት ላለማቋረጥ እየታገልን ነው እንጂ እስካሁን 3 የሚደርሱ ጤና ጣቢያዎች፣ ወደ 12 የሚደርሱ ጤና ኬላዎች አሁንም በየቀኑ በታጣቂ ኃይሎች ይዘረፋሉ።
° መጀመሪያ በስፋት #ፕላምፕሌት አልሚ ምግቦችን ሲወስዱ ነበር። እነርሱ ምግቦች ለሕፃናትና ለእናቶች ካልደረሱ ወደዛ መውሰድ አስፈላጊ አይደለም ብለን ስናስቆማቸው ጤና ኤክስቴሽኖችን እናንተ ናችሁ የደበቃችሁት አምጡ አስልኩ አይነት ነገር ማስፈራሪያ፣ ዛቻ፣ ድብደባዎች እያደረሱ ነው።
° ጋዝጊቭላና ድሀና ወረዳዎች አዚላ የሚባል ክላስተር አለ፣ በዚያ ስር ያሉ ጤና ኬላዎች፣ በጋዝጊብላ ወረዳ ደግሞ አዱፍቃ፣ አርካ ጤና ጣቢያዎች ስር ባሉ ጤና ኬላዎች ላይ ነው እንግልት እየተደረገ ያለው።
° የጤና አገልግሎቱ እየተቆራረጠ ነው። በቋሚነት እየተሰጠ አይደለም። ከአንድ እስከ ሶስት ቀናት በተከታታይ ይሰጣል። ከሆነ ጊዜ በኋላ ይመጡና እደገና ያቋርጡታል። ኮሚዩኒቲ ሰርቪስ የምንለው በጤና ኬላ ደረጃ የሚሰጠው ኦልሞስት እየቆመ ነው።
ለመፍትሄው ከማን ምን ይጠበቃል?
☑️ የአጋር ድርጅት ድጋፍ የተቀዛቀዘ ነው። ድጋፍ ማድረግ ቢችሉ የሰዎችን ሕይወት ይታደጋሉ። ከጸጥታው ጋር ተያይዞ ሊሆን ይችላል ኤኒይወይስ ስለ ረሀብ ደግሞም ስለ ህፃናት፣ ነፍሰጡር አጥቢ እናቶች ረሃብ ነው እያወራን ያለነው።
☑️ አይደለም እንደዚህ ድርቅ ተከስቶ አፍጦ መጥቶ ኖርማል በመደበኛ ሁኔታ እንኳ እንደዚህ ለይተናቸው የምግብ እጥረት እንዳለባቸው ሲታወቅ ወዲያውኑ ወደ ፕሮግራም ገብተው መታከም ያለባቸው ህፃናት ለተከታታይ 2 ወራት ምንም አልተደረገላቸውም።
ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
" ድርቁ በጣም እየባሰ ነው። መታከም ያለባቸው ህፃናት ለተከታታይ 2 ወራት ምንም አልተደረገላቸውም" - ዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ
በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ በዞኑ ስላሉ አሳሳቢ ጉዳዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
- ድርቁ በጣም #እየባሰ ነው። ባለፈው ጥናት ካጠናን በኋላ ሊደረግ የሚገባው ግን ያልተደረገ በጣም በስፋት ነው ያለው።
- የምግብ እጥረት እንዳለባቸው በተረጋገጠው መሠረት #ህፃናት #ነፍሰጡር፣ #አጥቢ እናቶች ወደ ተለያዩ ፕሮግራሞች ገብተው ሊደገፉ ነበር። እስቲል ማሟያ ምግብ በምንለው እጥረት እስካሁን ምንም አልተደረገላቸውም። እኛ #እየጮህን ነው። እስካሁን የመጣ፣ የተደረገ ድጋፍም የለም።
- በሌላ በኩል ድርቅ በተከሰተባችው አካባቢዎች አጠቃላይ የጤና መድህን የምንለው ፕሮግራም የአመት ክፍያው የሚያልቀው አሁን ነው። አልፎ ለማስከፈልም አልቻልንም። በጠቅላላ የጤና አገልግሎታቸው በጣም #የሚያሳዝን ሁኔታ እየገባንበት ያለንበት ሁኔታ ነው ያለው።
ምን ያህል ህፃናትና እናቶች ናቸው አሁን አስቸኳይ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው?
* በድርቅ የተጎዱት ወደ 33,000 የሚሆኑ ሰዎች ናቸው ከአንድ ወረዳ ብቻ። በአጠቃላይ እንደ ዞን በዚህ ድርቅ ተጎድተዋል ብለን የምናስባቸው ከ180,000 በላይ ህዝቦች ናቸው።
* ከእዚህ ውስጥ የሚበዙት ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች ናቸው። ወደ 7,000 ይደርሳሉ #ነፍሰጡርና አጥቢዎች ብቻ። ከአምስት ዓመት በታች #ህፃናት ኦልሞስት ወደ #18,000 አካባቢ ይደርሳሉ። እነዚህ ሁሉ አስቸኳይ ምግብ የሚፈልጉ ናቸው።
አቶ አሰፋ ታጣቂዎችን በተመለከተ ምን አሉ ?
° ታጣቂዎች የመጀመሪያ ታርጌታቸው ጤና ተቋማትን መዝርፍ ነው። እኛ አገልግሎት ላለማቋረጥ እየታገልን ነው እንጂ እስካሁን 3 የሚደርሱ ጤና ጣቢያዎች፣ ወደ 12 የሚደርሱ ጤና ኬላዎች አሁንም በየቀኑ በታጣቂ ኃይሎች ይዘረፋሉ።
° መጀመሪያ በስፋት #ፕላምፕሌት አልሚ ምግቦችን ሲወስዱ ነበር። እነርሱ ምግቦች ለሕፃናትና ለእናቶች ካልደረሱ ወደዛ መውሰድ አስፈላጊ አይደለም ብለን ስናስቆማቸው ጤና ኤክስቴሽኖችን እናንተ ናችሁ የደበቃችሁት አምጡ አስልኩ አይነት ነገር ማስፈራሪያ፣ ዛቻ፣ ድብደባዎች እያደረሱ ነው።
° ጋዝጊቭላና ድሀና ወረዳዎች አዚላ የሚባል ክላስተር አለ፣ በዚያ ስር ያሉ ጤና ኬላዎች፣ በጋዝጊብላ ወረዳ ደግሞ አዱፍቃ፣ አርካ ጤና ጣቢያዎች ስር ባሉ ጤና ኬላዎች ላይ ነው እንግልት እየተደረገ ያለው።
° የጤና አገልግሎቱ እየተቆራረጠ ነው። በቋሚነት እየተሰጠ አይደለም። ከአንድ እስከ ሶስት ቀናት በተከታታይ ይሰጣል። ከሆነ ጊዜ በኋላ ይመጡና እደገና ያቋርጡታል። ኮሚዩኒቲ ሰርቪስ የምንለው በጤና ኬላ ደረጃ የሚሰጠው ኦልሞስት እየቆመ ነው።
ለመፍትሄው ከማን ምን ይጠበቃል?
☑️ የአጋር ድርጅት ድጋፍ የተቀዛቀዘ ነው። ድጋፍ ማድረግ ቢችሉ የሰዎችን ሕይወት ይታደጋሉ። ከጸጥታው ጋር ተያይዞ ሊሆን ይችላል ኤኒይወይስ ስለ ረሀብ ደግሞም ስለ ህፃናት፣ ነፍሰጡር አጥቢ እናቶች ረሃብ ነው እያወራን ያለነው።
☑️ አይደለም እንደዚህ ድርቅ ተከስቶ አፍጦ መጥቶ ኖርማል በመደበኛ ሁኔታ እንኳ እንደዚህ ለይተናቸው የምግብ እጥረት እንዳለባቸው ሲታወቅ ወዲያውኑ ወደ ፕሮግራም ገብተው መታከም ያለባቸው ህፃናት ለተከታታይ 2 ወራት ምንም አልተደረገላቸውም።
ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
😭524❤75😢46😡26🕊24🙏6👏5🥰3
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዋግኽምራ " ድርቁ በጣም እየባሰ ነው። መታከም ያለባቸው ህፃናት ለተከታታይ 2 ወራት ምንም አልተደረገላቸውም" - ዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ በዞኑ ስላሉ አሳሳቢ ጉዳዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ? - ድርቁ በጣም #እየባሰ ነው። ባለፈው ጥናት ካጠናን በኋላ ሊደረግ የሚገባው ግን ያልተደረገ በጣም በስፋት…
#አማራ #ዋግኽምራ
በአማራ ክልል በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ሰሃላ ሰየምትን ጨምሮ ድርቅ በተከሰተባቸው ሌሎችም ወረዳዎች ላይ እንስሳት በመኖ እጥረት #እየሞቱ ፣ አካባቢያቸውን ለቀው #እየተፈናቀሉ መሆኑን አስተዳደሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።
የአስተዳደሩ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምህረት መላኩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፣ ከ10,000 በላይ የተለያዬ እንስሳት በውሃና በመኖ እጥረት ሞተዋል።
በአበርገሌ፣ በሮቢና፣ በበለቃ በላይኛው ተከዜ ተፋሰስ በተለይ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ነጻ ያልወጡ፣ መንግሥት የማይቆጣጠራቸው ቀበሌዎች ላይ ሰፋ ያለ ችግር እንዳለ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ በድርቁ ቀጥተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው ያሉ እንስሳትን በሚመለከት ኃላፊው ፤ በሦስቱም ወረዳዎች ፦
* ሰሃላ ሰየምት፣
* ዝቋላ፣
* አበርገሌ በጣም የቅድሚያ ቅድሚያ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የለተለዩ ወደ 791,000 አካባቢ እንደሆኑ አስረድተዋል።
ከ791,000ዎቹ ውስጥ በተለይ ሰሃላ ሰየምት ወረዳ ላይ ያሉት ክርቲካሊ የዕለትም አቅርቦት ስላጡ 171,000 ወደ ደሃና ወረዳ ተፈናቅለው እንዲሄዱና ተጠግተው ለጊዜው እንዲቆዩ መደረጉን ተናግረዋል።
" ይህን ይህል ተፈናቅሎ ከሄደ ቀሪው 620,000 ደግሞ ከዚያው #እየተላወሰ ነው ያለው " ሲሉ አክለዋል።
ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-24
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ሰሃላ ሰየምትን ጨምሮ ድርቅ በተከሰተባቸው ሌሎችም ወረዳዎች ላይ እንስሳት በመኖ እጥረት #እየሞቱ ፣ አካባቢያቸውን ለቀው #እየተፈናቀሉ መሆኑን አስተዳደሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።
የአስተዳደሩ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምህረት መላኩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፣ ከ10,000 በላይ የተለያዬ እንስሳት በውሃና በመኖ እጥረት ሞተዋል።
በአበርገሌ፣ በሮቢና፣ በበለቃ በላይኛው ተከዜ ተፋሰስ በተለይ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ነጻ ያልወጡ፣ መንግሥት የማይቆጣጠራቸው ቀበሌዎች ላይ ሰፋ ያለ ችግር እንዳለ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ በድርቁ ቀጥተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው ያሉ እንስሳትን በሚመለከት ኃላፊው ፤ በሦስቱም ወረዳዎች ፦
* ሰሃላ ሰየምት፣
* ዝቋላ፣
* አበርገሌ በጣም የቅድሚያ ቅድሚያ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የለተለዩ ወደ 791,000 አካባቢ እንደሆኑ አስረድተዋል።
ከ791,000ዎቹ ውስጥ በተለይ ሰሃላ ሰየምት ወረዳ ላይ ያሉት ክርቲካሊ የዕለትም አቅርቦት ስላጡ 171,000 ወደ ደሃና ወረዳ ተፈናቅለው እንዲሄዱና ተጠግተው ለጊዜው እንዲቆዩ መደረጉን ተናግረዋል።
" ይህን ይህል ተፈናቅሎ ከሄደ ቀሪው 620,000 ደግሞ ከዚያው #እየተላወሰ ነው ያለው " ሲሉ አክለዋል።
ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-24
@tikvahethiopia
😭451😢44❤37🕊12😱7🥰6🙏5😡4