TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" በክልሌ ውስጥ ምንም አይነት የማቆያ ካምፕ የለም " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት " በክልሌ ውስጥ ምንም አይነት የማቆያ ካምፕ የለም " አለ።

የክልሉ መንግሥት ይህንን ያለው ዛሬ ምሽት " የሀሰት መረጃ " በሚል በተረጋገገጠ የኮሚኒኬሽን ቢሮ የማህበራዊ ትስስር ገፁ በኩል ባወጣው አጭር የፅሁፍ መግለጫ ነው።

በዚህም ፅሁፉ ፤ " ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር ተያይዞ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት #በሸገር እና #ፊቼ ከተሞች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈፃፀም መርማሪ ቦርድ የማያውቃቸው የማቆያ ካምፕ እንዳለ ተደርጎ በአንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ ህዝብን የሚያደናግር ሃሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ  ይገኛል " ሲል ገልጿል።

ነገር ግን " በተጠቀሱ ከተሞችም ሆነ አጠቃላይ በክልላችን ምንም ዓይነት የማቆያ ካምፕ የለም " ሲል የክልሉ መንግሥት አሳውቋል።

@tikvahethiopia
👎2.79K👍65584😢38🕊33🙏32😱23🥰18