" በክልሌ ውስጥ ምንም አይነት የማቆያ ካምፕ የለም " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት
የኦሮሚያ ክልል መንግሥት " በክልሌ ውስጥ ምንም አይነት የማቆያ ካምፕ የለም " አለ።
የክልሉ መንግሥት ይህንን ያለው ዛሬ ምሽት " የሀሰት መረጃ " በሚል በተረጋገገጠ የኮሚኒኬሽን ቢሮ የማህበራዊ ትስስር ገፁ በኩል ባወጣው አጭር የፅሁፍ መግለጫ ነው።
በዚህም ፅሁፉ ፤ " ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር ተያይዞ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት #በሸገር እና #ፊቼ ከተሞች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈፃፀም መርማሪ ቦርድ የማያውቃቸው የማቆያ ካምፕ እንዳለ ተደርጎ በአንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ ህዝብን የሚያደናግር ሃሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል " ሲል ገልጿል።
ነገር ግን " በተጠቀሱ ከተሞችም ሆነ አጠቃላይ በክልላችን ምንም ዓይነት የማቆያ ካምፕ የለም " ሲል የክልሉ መንግሥት አሳውቋል።
@tikvahethiopia
የኦሮሚያ ክልል መንግሥት " በክልሌ ውስጥ ምንም አይነት የማቆያ ካምፕ የለም " አለ።
የክልሉ መንግሥት ይህንን ያለው ዛሬ ምሽት " የሀሰት መረጃ " በሚል በተረጋገገጠ የኮሚኒኬሽን ቢሮ የማህበራዊ ትስስር ገፁ በኩል ባወጣው አጭር የፅሁፍ መግለጫ ነው።
በዚህም ፅሁፉ ፤ " ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር ተያይዞ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት #በሸገር እና #ፊቼ ከተሞች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈፃፀም መርማሪ ቦርድ የማያውቃቸው የማቆያ ካምፕ እንዳለ ተደርጎ በአንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ ህዝብን የሚያደናግር ሃሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል " ሲል ገልጿል።
ነገር ግን " በተጠቀሱ ከተሞችም ሆነ አጠቃላይ በክልላችን ምንም ዓይነት የማቆያ ካምፕ የለም " ሲል የክልሉ መንግሥት አሳውቋል።
@tikvahethiopia
👎2.79K👍655❤84😢38🕊33🙏32😱23🥰18