TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኣሸንዳ

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የ #ኣሸንዳ በዓል ሲከበር እና ሲዘከር የተጀመረውን ሰላምን በማጠናከር እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።

ይህን ጥሪ ያቀረበው ዛሬ የኣሸንዳ በዓል ምክንያት በማድረግ በሰጠው መግለጫ ነው።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፤ " ኣሸንዳ ፣ ማርያ ፣ ዓይኒ ዋሪ የነፃነት የእኩልነት ተምሳሌት ፤ የሴቶች የአብሮነትና የአንድነት ምልክት በመሆን ፤ የትግራይ ክብርና እሴቶች በቅብብሎሽ የትውልዶች ማስተሳሰርያ ገመድ እንዲሆኑ የራሱ አስተዋፅኦ አድርገዋል እያደረገም ይገኛል " ብሏል።

ባለፉት አመታት በነበረው ጦርነት ምክንያት የትግራይ ሴቶች እንደ አሸንዳ የመሰሉ የአደባባይ በአላት በደስታና ፌስታ ሊያከብሩት ይቅርና ፀሃይ ወጥታ ሳለች ጨልሞባቸው ደግሞ ለመተረትክ የሚከብድ ግፍ እንደደረሰባቸው ገልጿል።

" ይሁን እንጂ ግፉ እንዲቆም በፅናት በመታገላችሁ እና በማታገላችሁ ቢያንስ አሁን ለተደረሰው ደረጃ ለመድረስ መተኪያ የሌለው ተግባር ፈፅማቹሃል " ያለው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፤ " አስተዳደሩና ህዝቡ በናንተ ኩራት ይሰማዋል " ብሏል።

በዓሉ ሲከበር እና ሲዘከር የተጀመረው ሰላም በማጠናከር ፣ የህዝብ ጥያቄዎች እና ፍላጎቶች ፣ በሰላማዊና ፓለቲካዊ ትግል ለመመለስ በሚደረገው ትግል አሁንም እንደትናንት በፅናት እንደምትታገሉ በመታመመን ነው ብሏል።

" ያለው ሁኔታ ከባድ ነው " የሚለው አስተዳደሩ " ተፈናቃይ ወገኖች አጅግ በከፋ የኑሮ ሁኔታ ላይ ነው ያሉት ፣ በአማራና ኤርትራ ታጣቂ ሃይሎች ስር የሚገኝ ህዝባችን ማለቅያ የሌላቸው ግፎች እየተፈፀሙበት ነው ፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጥር ህዝባችን በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ ይገኛል " ብሏል።

የትግራይ ሴቶች ይህን የመሰለ ከባድ ሁኔታ ተቋቁማችሁ የአሸንዳ ፣ ማሪያ ፣ ዓይኒ ዋሪ በዓል ለማክበር መቻላችሁ መንፈሳዊ ጥንካሬአችሁ ብርቱና ከፍተኛ መሆኑ ማሳያና ማረጋገጫ ነው ሲል ገልጿል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ጥያቄዎች በሰላማዊና ፓለቲካዊ ትግል እንዲመለሱ እጅግ እልህ አስጨራሽ ትግል እያካሄደ መሆኑን ገልጾ " አሁንም ተፈናቃይ ወገኖች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ፣ በትግራይ መሬት የሚገኙ የአማራና የኤርትራ ታጣቂዎች ለቀው እንዲወጡ ፣ የተቋረጠው ሰብአዊ አርዳታ እንዲጀምር ፣ ወንጀለኞች በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ያላሰለሰ ትግል አካሂዳለሁ " ብሏል።

@tikvahethiopia
👍655👎26882🕊24🙏9👏5🥰4😢3😱2
TIKVAH-ETHIOPIA
በአዲስ አበባ የኣሸንዳ በዓል መቼ ይከበራል ? የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፤ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ የ2015 ዓ.ም የአሸንዳ በአል አከባበር መርሃ ግብር ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሰረት፤ በዓሉን #ነሃሴ_28 ቀን 2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ለማክበር እቅድ መያዙ ገልጿል። የሚደረግ የጊዜ ለውጥ ካለ አስቀድሞ የሚገለፅ መሆኑንም አስተዳደሩ አሳውቋል። የበዓሉ መርሀግብር ምን ይመስላል ? - ነሃሴ 13…
ፎቶ ፦ ዛሬ ነሃሴ 15 ቀን 2015 ዓ/ም የ #ኣሸንዳ በዓልን ምክንያት በማድረግ በመቐለ ከተማ የጎደና የካርኒቫል ትርኢትና ሰማእታት የሚያስታውስ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት ተከናውኗል።

#ማስታወሻ ፦ ከ " ኣሸንዳ " አከባበር ጋር በተያያዘ በክልሉ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ የወጣው መርሀ ግብር ከላይ ተያይዟል። በቢሮው ከተገለፀው ውጭ የሚካሄደ የአሸንዳ በዓል ዝግጅት እውቅና እንደሌለው ተነግሯል።

Photo Credit : Demtsi Weyane

@tikvahethiopia
495👎321👍291🕊35🥰11👏11😢9🙏8😱6
TIKVAH-ETHIOPIA
የዘንድሮው የኣሸንዳ ፣ ማርያ ዓይኒ ዋሪ በዓል እንዴት እየተከበረ ነው ? የኣሸንዳ ፣ ማርያ ዓይኒ ዋሪ በዓል ካለፉት ዓመታት እጅግ በተሻለ ድምቀት በትግራይ እንዲሁም በሌሎች አካባቢዎች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። በዓሉ በዋነኝነት ትግራይ ውስጥ እጅግ በደመቀ ሁኔታ በመከበር ላይ ነው። ከእሁድ ነሃሴ 13/2015 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ መከበር የጀመረው በዓሉ ፤ ነሃሴ 13 ና 14 / 2015 ዓ.ም በዓዲግራት…
#ኣሸንዳ

የዘንድሮው የኣሸንዳ በዓል ወደ አለፍነው ጦርነት ያስገቡን ስህተቶች ላለመደግም ቃል የምንገባበት ነው ሲሉ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።

" ባለፉት ሁለት ሶስት የጦርነት አመታት በትግራይ ሴቶች የደረሰው ግፍ አሰቃቂ ነው። " ያሉት አቶ ጌታቸው  " የትግራይ ሴቶች ሰላምና ስቃይ የትግራይ ህዝብ ሰላምና ስቃይ ነው። " ብለዋል።

" ከሶስት አመታት በፊት የአሸንዳ በዓል ከተጫወቱት ቆነጃጂት በጦርነት ምክንያት  አካላቸው የጎደሉ የተሰው አሉ " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ይህንን እንዳይደገም በሚደረገው ትግል የሴቶች ተሳትፎ ከፍተኛ ነው። " ሲሉ አስገንዝበዋል።

ሴቶች ተውበው የአሸንዳ በዓል ሲያከብሩ ኤችአይቪ ኤድስ የመሰሉ ተላላፊ በሽታዎች መዘንጋት እንደሌለባቸው አሳስበዋል።

" በዓሉ ተፋናቃይ ህዝባችን ወደ ቀድመው ቄየው የሚመለስበት ፣ ስቃይ ውስጥ የሚገኘው ህዝባችን ነፃ እንዲሚወጣ ገሃድ የሚሆንበት እንደሚሆን እንተማመናለን " ብለዋል።

@tikvahethiopia
👍730👎31066🕊37🥰12😢11👏8😱7🙏3
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሃሳብ ልዩነቱ ወደ ግጭት አያመራም " - አቶ ጌታቸው ረዳ ዓመታዊው የ2016 ዓ/ም የአሸንዳ በዓል ዛሬ ነሃሴ 16/2016 ዓ/ም በመላ ትግራይ መከበር ጀምሯል። በዓሉ እስከ ነሃሴ 24/2016 ዓ.ም አንደሚቀጥል የወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል። በሌላ በኩል ፕሬዜዳንት ጌታቸው በ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር የተገነባ የ10.2 ኪሎ ሜትር  የአስፋልት መንገድ ሲመርቁ ፤ የአሸንዳ አደባባይ ግንባታ መሰረተ…
#ኣሸንዳ

ከሰሞኑን በፖለቲካ ትኩሳት ውስጥ የከረመችው ትግራይ በደማቅ ሁኔታ የዘንድሮውን የኣሸንዳ በዓል እያከበረች ነው።

በዓሉን ለማክበር በርካታ እንግዶች ትግራይ ይገኛሉ።

በዓሉ እስከ ነሃሴ 24 ቀን 2016 ዓ/ም በተለያዩ ስነስርዓቶች እየተከበረ ይቀጥላል።

በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የሚከበረው የኣሸንዳ በዓል ፍቅር፣ ይቅር ባይነትና መልካም ተግባቦት በተግባር የሚንጸባረቅበት በዓል ሲሆን በዓሉ በልጃገረዶች ይበልጥ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበረል።

ልጃገረዶች አደባባይ ወጥተው ይህን በዓልን በድምቀት ያከብራሉ።

የበዓሉ ይዘት በዋናነት ህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ መልካም ተግባቦቶች፣ ፍቅርንና ይቅር ባይነት ላይ ያነጣጠረ ነው።

የሌሎች ሃሳቦች፣ ጭፈራዎች እና ትእይንቶች እንዲታዩ የሚጋብዝ በዓል ከመሆኑም ባለፈ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት አይንፀባረቅበትም።

ፎቶ፦ ትግራይ ቲቪ (ኖርዘርን ስታር ሆቴል፣ መቐለ ነሐሴ 17)

#Ashenda #Tigray

@tikvahethiopia
495🕊49😡28🥰23🤔13🙏12😢11😱4😭1