TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አብን

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ በዛሬው ዕለት በአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ላይ መግለጫ አውጥቶ ነበር።

አብን በዚህ መግለጫው ፤ በየትኛውም አሰላለፍ እና አግባብ ስለአማራ ህዝብ የተሰለፉ ሀይሎች #ጦርነት ዘላቂ ጥቅምን ለማረጋገጥ አስቻይ እንዳልሆነ ሊገነዘቡት ይገባል ብሏል።

ይልቁን ጦርነት ህዝብን ለተደራራቢ የማህበራዊ ፣ ሰብአዊና ኢኮኖሚያዊ ድቀት ስለሚዳርግ ለሰላማዊ የፖለቲካ መፍትሄዎች ተገቢውን ስፍራ ሰጥተው ለክልሉ ሰላም መመለስ  ድርሻቸውን እንዲወጡ ሲል ጥሪ አቅርቧል።

" የአማራ ህዝብ ከሌላው የሀገሪቱ ህዝብ ጋር ያለውን የወንድማማችነት እሴቶች ከሚንዱ ቅስቀሳዎች ፣ በራሱ እና በልጆቹ የተመሰረቱ ተቋማትን በተለይም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከሚያጠለሹ መልዕክቶች እንዲሁም የአማራ ህዝብ ማህበራዊ ረፍት እንዲያጣ ከሚመኙ አካላት በስልት የሚሰጡትን አጀንዳዎች በመጸየፍ ወደ ሰላም መድረክ የሚያመሩ መንገዶችን ሁሉ ለመጥረግ አቅሙ የፈቀደውን ርብርብ እንዲያደርግ " ሲል አብን አሳስቧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
👎1.31K👍1.17K90🕊82👏12😢9🥰8😱1
#አብን

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ምክትል ሊቀመንበር ከኃላፊነታቸው ለቀቁ።

የአብን ምክትል ሊቀመንበር መልካሙ ሹምዬ በገዛ ፍቃዳቸው ከድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበርነት እና የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት መልቀቃቸውን ለፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ በፃፉት ደብዳቤ አሳውቀዋል።

ለምን እዚህ ውሳኔ ላይ ደረሱ ?

መልካሙ ሹምዬ ፤ በእስካሁኑ ቆይታቸው በግል እና በድርጅት ሥራዎች ያጋጠሙ ፈተናዎችን ለመቋቋም የበኩላቸውን ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

ነገር ግን ከአብላጫው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ጋር ያላቸው የአቋም ልዩነት እየሰፋ መሆዱን ጠቁመዋል።

የሃሳብ እና የአቋም ልዩነቱ ከሕዝቡን መብት ፣ ጥቅም እና ኅልውና መከበር አንጻር ያለው ትርጉም እና ውጤት ከፍ ያለ መሆኑን እንዳመኑበት ፤ በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውስጥ አሁን ካለው ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር በኃላፊትነት መቀጠል የድርጅቱንና የሕዝቡን ጥቅም የሚያስከብር ሆኖ ባለማግኘታቸው ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን አሳውቀዋል።

መልካሙ ሹምዬ ምንም እንኳን ከኃላፊነት በገዛ ፍቃዳቸው ቢለቁም የድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ #አባልነታቸውን ይዘው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጻዋል።

@tikvahethiopia
👍1.54K👎176106🕊42😱26🙏16😢12👏9🥰6