TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የጋራ መግለጫ ምን ይላል ? የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኬንያ ያስራ ጉብኝትን እና ከፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ያደረጉትን ምክክር ተከትሎ የኬንያ " ስቴት ሀውስ " የጋራ ነው ያለውን መግለጫ ዛሬ ምሽት አውጥቷል። በዚህም መግለጫ ፤ ፕሬዚዳንት ሩቶ እና ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ ከአፍሪቃ ቀንድ ደህንነት…
#ኢትዮጵያ #ኬንያ #ታንዛኒያ
በኬንያ ናይሮቢ ለ2 ቀን የስራ ጉብኝት ያደረጉት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ደግሞ ወደ ታንዛኒያ አቅንተዋል።
በታንዛኒያ የሶስት ቀን የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ ተብሏል።
በሌላ በኩል ደግሞ ፤ የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በኬንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ተነግሯል።
ኢታማዦር ሹሙ ፤ ከኬንያው አቻቸው ጄኔራል ፍራንሲስ ኦሞንዲ ኦጎላ ጋር የሁለቱን ሀገራት ትስስር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ተገልጿል።
በወታደራዊ መሪዎቹ መካከል በተካሄደ ውይይት የቀጣናውን ደህንነት ማስጠበቅ፣ የመከላከያ ትብብር እና የጋራ ስልጠና ልምምዶችን ማሳደግ የሚሉት ተነስተዋል ተብሏል።
@tikvahethiopia
በኬንያ ናይሮቢ ለ2 ቀን የስራ ጉብኝት ያደረጉት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ደግሞ ወደ ታንዛኒያ አቅንተዋል።
በታንዛኒያ የሶስት ቀን የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ ተብሏል።
በሌላ በኩል ደግሞ ፤ የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በኬንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ተነግሯል።
ኢታማዦር ሹሙ ፤ ከኬንያው አቻቸው ጄኔራል ፍራንሲስ ኦሞንዲ ኦጎላ ጋር የሁለቱን ሀገራት ትስስር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ተገልጿል።
በወታደራዊ መሪዎቹ መካከል በተካሄደ ውይይት የቀጣናውን ደህንነት ማስጠበቅ፣ የመከላከያ ትብብር እና የጋራ ስልጠና ልምምዶችን ማሳደግ የሚሉት ተነስተዋል ተብሏል።
@tikvahethiopia
😡429❤318👏38🥰24🙏15😭14🕊11😱6😢5
በምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር #ታንዛኒያ ለሳምንታት በዘለቀ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት 155 ሰዎች ሲሞቱ ፤ 236 ሰዎች ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት እንደደረሰባቸው የሀገሪቱ ጠ/ሚ ቃሲም ማጅዋሊ ተናግረዋል።
በዚህ ሳምንት በጎረቤት #ኬንያ በደረሰው የጎርፍ አደጋ በትንሹ 35 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል። 40,000 ሰዎች ደግሞ ከቤታቸው እንዲፈናቀሉ ሆነዋል።
@tikvahethiopia
በዚህ ሳምንት በጎረቤት #ኬንያ በደረሰው የጎርፍ አደጋ በትንሹ 35 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል። 40,000 ሰዎች ደግሞ ከቤታቸው እንዲፈናቀሉ ሆነዋል።
@tikvahethiopia
😭387😢69❤40🙏24😱16🕊6🥰2