TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ድርድር ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ስለ #ድርድር ምንድነው ያሉት ? " ከኦነግ ሸኔ ጋር የሚደረገው ድርድር ከነገ ወዲያ በታንዛኒያ ይጀመራል። ይህንን ድርድር የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህዝብ አብዝቶ ይፈልገዋል። በዚህ ድርድር የሚሳተፉ ወገኖች ሁሉ የዛሬዋን ቀን እያሰቡ ፣ ከግጭት፣  ከጦርነት እንደማናተርፍ አውቀው ህግ እና ስርዓት ተከትለን ይቅር ተባብለን ሀገራችንን በጋራ ማነፅ እና መገንባት…
#ታንዛኒያ

የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ዛሬ #ታንዛኒያ ገብተዋል።

አቶ ደመቀ በ4 የአፍሪካ ሀገራት ጉብኝት ያደርጋሉ የተባለ ሲሆን የመጀመሪያውን ጉብኝታቸውን በታንዛኒያ ጀምረዋል።

ከታንዛኒያ በመቀጠል በኮሞሮስ ፣ ቡሩንዲ እና ዩጋንዳ ጉብምት ያደርጋሉ ተብሏል።

አቶ ደመቀ ዛሬ ታንዛኒያ ከገቡ በኃላ #በዛንዚባር የሚገኘውን የአፄ ኃይለሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።

አቶ ደመቀ መኮንን ወደ ታንዛኒያ ለጉብኝት ያመሩት ትላንት የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ " ኦነግ ሸኔ " ሲሉ ከተጠሩት የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር መንግሥት ነገ በታንዛኒያ ድርድር እንደሚጀምር ካሳወቁ በኃላ ነው።

አቶ ደመቀ የታንዛኒያ ጉዟቸው በ4 የአፍሪካ ሀገራት ለሚያደርጉት ጉብኝት የመጀመሪያ ሀገር ከመሆኑ በዘለለ ይደረጋል ከተባለው ድርድር ጋር ይገናኝ እንደሆነ ወይም በዚህ ድርድር ላይ ይገኙ/አይገኙ የታወቀም ሆነ ይፋ የተደረገ መረጃ #የለም

@tikvahethiopia
👍629👎45057🕊41🙏13🥰8😢8😱4
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የጋራ መግለጫ ምን ይላል ? የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኬንያ ያስራ ጉብኝትን እና ከፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ያደረጉትን ምክክር ተከትሎ የኬንያ " ስቴት ሀውስ " የጋራ ነው ያለውን መግለጫ ዛሬ ምሽት አውጥቷል። በዚህም መግለጫ ፤ ፕሬዚዳንት ሩቶ እና ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ ከአፍሪቃ ቀንድ ደህንነት…
#ኢትዮጵያ #ኬንያ #ታንዛኒያ

በኬንያ ናይሮቢ ለ2 ቀን የስራ ጉብኝት ያደረጉት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ደግሞ ወደ ታንዛኒያ አቅንተዋል።

በታንዛኒያ የሶስት ቀን የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ ተብሏል።

በሌላ በኩል ደግሞ ፤ የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በኬንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ተነግሯል።

ኢታማዦር ሹሙ ፤ ከኬንያው አቻቸው ጄኔራል ፍራንሲስ ኦሞንዲ ኦጎላ ጋር የሁለቱን ሀገራት ትስስር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ተገልጿል።

በወታደራዊ መሪዎቹ መካከል በተካሄደ ውይይት የቀጣናውን ደህንነት ማስጠበቅ፣ የመከላከያ ትብብር እና የጋራ ስልጠና ልምምዶችን ማሳደግ የሚሉት ተነስተዋል ተብሏል።

@tikvahethiopia
😡429318👏38🥰24🙏15😭14🕊11😱6😢5
በምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር #ታንዛኒያ ለሳምንታት በዘለቀ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት 155 ሰዎች ሲሞቱ ፤ 236 ሰዎች ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት እንደደረሰባቸው የሀገሪቱ ጠ/ሚ ቃሲም ማጅዋሊ ተናግረዋል።

በዚህ ሳምንት በጎረቤት #ኬንያ በደረሰው የጎርፍ አደጋ በትንሹ 35 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል። 40,000 ሰዎች  ደግሞ ከቤታቸው እንዲፈናቀሉ ሆነዋል።

@tikvahethiopia
😭387😢6940🙏24😱16🕊6🥰2